በክርስቶስ ወንጌል አላፍርም ያለው ጳውሎስ፣ ወንጌል ለማዳን የእግዚብሔር ኀይል እንደ ሆነ ይገልጻል። ከዚህ ጋር አያይዞም በ (ሮሜ 1:17)… ላይ፦ "በወንጌል የእግዚአብሔር ጽድቅ ተገልጧልና፤ ጽድቁም ከመጀመሪያ እስከ መጨረሻ በእምነት የሆነ ነው፣ “ጻድቅ በእምነት ይኖራል” ተብሎ እንደ ተጻፈ" "For in it the righteousness of God is revealed from faith to faith; as it is written, “The just shall live by faith.” (KJV) ሐዋሪያው በወንጌል የእግዚአብሔር ጽድቅ "ከእምነት ወደ እምነት ይገለጻል" ሲል ምን ማለቱ ነው? አንተ ከእምነት ወደ እምነት" የተባለው ቃል አያሌ ትርጉሞች አሉት ካልክ በኋላ ሁሉን ማብራራት ሰለማይቻል ስድስቱን አቅርበህ አብራርተሃል። ከጥልቅ ዳሰሳ በኋላ ከመጀመሪያው የእምነት ደረጃ ከፍ ወዳለው የእምነት ደረጃ ማለፍ ነው ብለህ ከካልቪን ፍቺ ጋር እንደምትስማማ ገልጸሃል። በተለያዩ ጊዚያት ቅዱሳን አባቶች የተለያየ ትርጉም ሰጥቷል ቅዱስ አጉስጦስ "በመንፈስና በፊደል" በሚል መጽሐፋቸው በምዕራፍ 11 ላይ "from the faith of those who confess it to the faith of those who prove it by their obedience" በማለት ገልጸውታል። ቡርገስ (Burgos) ቃሉን እንደሚከተለው ተርጎመውታል "from the faith of the synagogue (as a starting point) to the faith of the church (as a finishing point) ማርቲን ሉተር እንዲህ ተርጉመውታል፦ "the phrase from 'faith to faith' have been interpreted in various ways. Lyra gives the meaning; 'from unformed faith to formed faith'; but I do not believe it possible to believe for anyone to believe by unformed faith. Others explian the words thus 'from faith to faith of the Old Testament to the faith of new testament'; this exposition may be accepted; though it may be contested; it cannot possibly mean the righteous man lives by the faith his ancestors. The fathers had the same faith as we: there is only one faith; though it may have been less clear to them. "The words evidently mean: the righteousness of God is entirly from faith; but in such a way that there is constant growth and greater clarity… as 2 Cor 3:18; 'we are changed from glory to glory; and Psalm 84:7 'they go from strength to strength. Just so the words 'from faith to faith' signify that the believer grows in faith more and more. Likewise 'He that is righteous can be justified still' Rev 22:11; so that none should think that he has apprehended; and hence ceases to grow" "ከእምነት ወደ እምነት" የሚለውን ሃረግ ጆን ካልቪን እንደሚከተለው አብራርተውታል፦ "But instead of the expression used before by the apostle he now says 'from faith; for righteousness is offered by the gospel; and is received by faith". ካሉ በኋላ "to faith" በማለት አክለውበታል። ቀጥለውም "for as our faith makes progress; and; and as it advances in knowledge; so the righteousness of God increases in us at the same time at the same time; and the the possessiob of it is in a manner confirmed. When at first we taste the gospel; we indeed see God's countenance turns towards turned towards us; but at a distance: the the knowledge of true religion grows in us; by coming as it were nearer; we behold God's favour more clearly and more familiiarly. (Commentery ob the Epistle to the Romans) ሉተርና ካልቪን "ከእምነት ወደ እምነት"የሚለው ሃረግ በአንድ አማኝ ዘንድ የሚሆን የእድገት ለውጥ ነው ብሏል። ከዚህ በተጨማሪ ካልቪን "እምነት ሲጨምርና፣ በእውቀት ሲያድግ፣ ከዚህ በተጓዳኝ የእግዚአብሔር ጽድቅ በእኛ ውስጥ ይጨምራል" ብሏል። ካልቪን የእግዚአብሔር ጽድቅ በአማኙ ይጨምራል ብለው ካንዱ የእምነት ደረጃ ከፍ ወዳለ ወዳለ ወደ ሌላ የእምነት ደረጃ ጋር ማጎዳኛቸው ከፍተኛ ሕጸጽ አለው። ሲጀምር ጽድቅ ለአማኙ የሚቆጠርለት "imput" እንጂ በአማኝ ውስጥ የሚቀመጥ (impart) አይደለም። ቅድስና ይሰርጻል፣ ጽድቅ ደግሞ ይቆጠራል። Sanctification is "imparted" while righteousness is 'imputed" መጽሐፍ ቅዱስ ጽድቅ ይቆጠራል ይላል እንጂ (imparted) ወይም ይሰርፃል አይልም። ከዚህ በተጨማሪ የእግዚአብሔር ጽድቅ ይጨምራል ወይም ያድጋል ብሎ ማቅረብም ስህተት ነው። ስለዚህ ከካልቪን comment ሦስት አበይት ግድፈቶች ማየት ይቻላል። እነዚህም፦ 1) ጽድቅ ይቆጠራል እንጂ በአማኙ ውስጥ ሰራጺ እንዳልሆነ፣ 2) ጽድቅ የማይጨምርና የማይቀንስ እንደ ሆነ፣ 3) ጽድቅ በአማኙ ውስጥ የማይኖር መሆኑ ነው። ከዚህ ቀጥሎ "በወንጌል የእግዚአብሔር ጽድቅ ከእምነት ወደ እምነት ተገልጧል" የሚለው ሃቲት exegesis ፈታ አድርጌ ለማቅረብ እሞክራለሁ። ከዚያ በፊት ግን ኢየስሱ እንደ ፍጹም ሰውነቱ ከኀጢአት ውጭ ሙሉ ሰው ነውና በምድር በትሥግብት በነበረበት ጊዜ "እምነት" ነበረው ወይ? የሚለው ጥያቄ መመለስ ያስፈልጋል። በንጉሥ ጄምስ የመጽሐፍ ቅዱስ ትርጉም አራት ጊዜ "የኢየሱስ ክርስቶስ እምነት" "The faith of Jesus Christ" ተብሎ የተጻፈው በዘመናዊ ቅጅዎች "ኢየሱስን በማመን" ተብለው ተተርጉሟል። ዘመናዊ ቅጅዎች "በወንጌል የእግዚአብሔር ጽድቅ ከእምነት ወደ እምነት ተገልጧል" ተብሎ የተጻፈው እንዴት እንደ ለወጡት እንይ፦ "በወንጌል የእግዚአብሔር ጽድቅ ተገልጧልና፤ ጽድቁም ከመጀመሪያ እስከ መጨረሻ በእምነት የሆነ ነው፣ “ጻድቅ በእምነት ይኖራል” ተብሎ እንደ ተጻፈ" "ከእምነት ወደ እምነት" የሚለው "ጽድቁም ከመጀመሪያ እስከ መጨረሻ በእምነት የሆነ ነው" ተብሎ እንደ ተቀየረና የራስ አተረጓጎም እንደታከለበት ማየት ይቻላል። ይ ቀ ጥ ላ ል መልስ ግን እሻለሁ!
ምርጫው ፐርሰናል ወይስ አጠቃላይ ከእስራኤል አንጻር? በ H G L መፍታት ይኖርብናል እንዲሁም ከ tulip በፊት how to reconcile free will and God for knowledge its need philosophical argument .