ግጥም/Lyrics
ሃሌ ሃሌሉያ |4x|
ሁሉን የሚገዛ ጌታ ነግሧል
አምልኮ ውዳሴ ይገባዋል
ቅዱስነት ግርማ በፊቱ አለ
ማስፈራቱ ክብሩ የተለየ
ክብር ክብር የተረፈው
ሞገስ ምገስ የበቃው
ትልቅ ነው ትልቅ ነው
በትልቅነቱ ላመስግነው
1.ክብሩ አይመዘን በምንም አይለካ
ዘማይ ዙፋኑ ነው ምድር የእግሩ መርገጫ
ጥበብ ዕውቀቱ ከቶ አይቆጠር
ኢየሱስ ታላቅ ነው ብቻውን ከፍ ይበል
ቅዱስ ቅዱስ ያለ እና የነበረው
ቅዱስ ቅዱስ በክብር የሚመጣው
ቅዱስ ቅዱስ ልበለው ጌታዬ አምላኬን
ቅዱስ ቅዱስ የተባረከው ተስፋዬን
2. ምሕረቱ በእኔ ላይ ፀንታለች ልዘምር
ስሙን ላሞጋግሰው በህያዋን ምድር
ስዕለቴን በፊቱ እፈፅመዋለሁ
በየቀኑ ሁሉ እባርከዋለሁ
በምስጋናዬ ከፍ ከፍ ከፍ
በአምልኮዬ ከፍ ከፍ ከፍ ይበል
በሽብሸባዬ ከፍ ከፍ ከፍ
በእልልታዬ ከፍ ከፍ ከፍ ይበል
ይኸው ዜማዬ ለክብሩ መዝሙር
ተከብሮ ለአለው ለሌለው ፍጻሜ
ክብሬ ትዘምር ዝም እንዳትል ከቶ
በንጉሤ ፊት አላስቀር አምልኮ
ይንገሥ እላለሁ ዛሬም ደግሜ
ይባረክልኝ ጌታዬ አምላኬ
3. ላምልከው ኢየሱስን እንደ አምላክነቱ
ላንሳ በገናዬን ልደርድር በፊቱ
የዳዊትን ቅኔ ላዚም ልዘምር
እርሱን ለማመስገን የለኝም ገደብ
ቅዱስ ቅዱስ...
በምስጋናዬ ከፍ...
3 окт 2024