Тёмный

ስንቶቻችን ነን እግዚኦ መሐረነ ክርስቶስ ወይም በእንተ እግዚተነ ማርያም 12 ግዜ በትክክል የምንለው ?ትርሙንስ? 

ቤተ እግዚአብሔር
Подписаться 7 тыс.
Просмотров 22 тыс.
50% 1

ለምን ?? [12] ጊዜ እግዚኦ መሐረነ ክርስቶስና በእንተ እግዝእትነ ማርያም. እንላለን።
___________________________
በቤተክርስቲያናችን ሥርዓት ሁል ጊዜ ካህኑ እግዚአብሔር ከታሰራችሁበት የኃጥያት ማሠሪያ ይፍታችሁ ሲል [12] ጊዜ እግዚኦ መሐረነ ክርስቶስና [12] ደግሞ በእንተ እግዝእትነ ማርያም መሐረነ ክርስቶስ ያስብላል። ካህናትና ምዕመናን በሙሉ በጣቶቻችን እየቆጠርን ይህንኑ [12] ጊዜ እንላለን።
እግዚኦ መሐረነ ክርስቶስ ማለት፦ አቤቱ ክርሰቶስ ማረን ሲሆን በእንተ እግዝእትነ ማርያም መሐረነ ክርስቶስ ደግሞ ስለ እመቤታችን ማርያም ብለህ ክርሰቶስ ማረን ማለት ነው።
አስራ ሁለት ጊዜ እግዚኦ መሐረነ መባሉ ለቀኑ 12 ሰዓት በእንተ እግዝእትነ ማርያም ደግሞ ለሌሊቱ 12 ሰዓት ሲሆን በአጠቃላይ በየሰዓቱ ለሠራነው ኃጥያት ለሃያአራቱ ፳፬ [24ቱ] ሰዓት ምሕረትን እናገኝ ዘንድ ነው።
ሌላው አሥራ ሁለት ጊዜ የሆነበት ምክንያት ፦
፩ኛ. በስመ ሥላሴ ነው። በእያንዳንዱ ፊደል
_____________________________
አ ብ ወ ል ድ መ ን ፈ ስ ቅ ዱ ስ
፩ ፪ ፫ ፬ ፭ ፮ ፯ ፰ ፱ ፲ ፲፩ ፲፪
____________________________
፪ኛ. የድኃነታችን ምክንያት በሆነችው በእመቤታችን ስም ፊደል
_______________________________
ቅ ድ ስ ት ድ ን ግ ል ማ ር ያ ም
፩ ፪ ፫ ፬ ፭ ፮ ፯ ፰ ፱ ፲ ፲፩ ፲፪
_____________________________
አቆጣጠሩም እግዚኦ መሐረነ ሲባል በአውራጣት እየቆጠሩ ከጠቋሚ ጣት ወደታች ቀጥሎ በመሐል ጣት ወደ ላይ ከዚያም በቀለበት ጣት ወደ ታች ተደርጎ በማርያም ጣት [በትንሿ] ጣት ወደላይ ነው።
_____________________________
ከጠቋሚ ጣት ወደ ታች ፦ አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ እኛን ለማዳን ከሰማየ ሰማያት መውረዱን በዚህ ምድር መመላለሱን ሕማሙንና ሞቱን እናስባለን።
_____________________________
መሐል ጣት ወደላይ ፦ ማረጉን ወደ ሰማይ መውጣቱን
_____________________________
በቀለበት ጣት ወደታች ስንቆጥር፦ ለፍርድ መምጣቱን
______________________________
በትንሿ ጣት ወደላይ ስንወጣ፦ ደግሞ ሁላችንን በትንሳኤ ዘጉባኤ ይዞን ወደ ሰማይ እንደሚያወጣን እያሰብን ነው።
______________________________
በእንተ እግዝእትነ ማርያም ስንል አቆጣጠሩ፦ ከትንሽ ጣት ወደ ታች ይጀመርና በጠቋሚ ጣት ወደላይ ይፈፀማል። ይህም እመቤታችን ድንግል ማርያም ከትሕትና ወደ ልዕልና ከፍ ማለቷን የሚያሳየን ምስጢር ነው።
______________________________
ምንጭ ከመጽሀፈ አሚን ወሥርዓት የተወሰደ
በመምህር ዶ/ር ዘበነ ለማ ተፃፈ

Развлечения

Опубликовано:

 

10 фев 2022

Поделиться:

Ссылка:

Скачать:

Готовим ссылку...

Добавить в:

Мой плейлист
Посмотреть позже
Комментарии    
Далее
🤲❤ጸሎት ባርቶስ የሀሙስ🙏🤲
17:03
Они нас подслушивают😁
0:52
Просмотров 3,3 млн
Моя Жена Босс!
0:40
Просмотров 2,4 млн