Тёмный

በአዲስ አበባ የሚገኙ ሆቴሎች ለኢሬቻ በዓል እንግዶች እስከ 40 በመቶ የሚደርስ ቅናሽ ሊያደርጉ ነው| Ethiopia | Addis Ababa| Irrecha 

Подписаться
Просмотров 502
% 21

በመጪው ቅዳሜ በአዲስ አበባ የሚከበረውን ዓመታዊውን የኢሬቻ በዓል ለሚታደሙ እንግዶች፤ በከተማይቱ የሚገኙ ሆቴሎች እስከ 40 በመቶ የሚደርስ ቅናሽ ሊያደርጉ ነው። የአዲስ አበባ ባህል፣ ኪነ ጥበብ እና ቱሪዝም ቢሮ ለበዓሉ ቅናሽ የሚያደርጉ ሆቴሎች ዝርዝር እንዲገለጽለት ባለፈው ሳምንት ጥያቄ ማቅረቡም ተነግሯል።
ቢሮው ጥያቄውን ያቀረበው 170 ሆቴሎችን በአባልነት ለያዘው የአዲስ አበባ ሆቴል ባለንብረቶች ማህበር መሆኑን የማህበሩ ፕሬዝዳንት ወ/ሮ አስቴር ሰለሞን ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናግረዋል። ይህንኑ ተከትሎ ማህበሩ ለአባላቱ ለኢሬቻ በዓል ቅናሽ እንዲያደርጉ መልዕክት ማስተላለፉን ገልጸዋል።
በበዓላት ወቅት ወደ ሀገር ውስጥ የሚገቡ እንግዶችን ታሳቢ በማድረግ ሆቴሎች ቅናሽ ማድረጋቸው የተለመደ መሆኑን የሚያስረዱት ወ/ሮ አስቴር፤ ለኢሬቻ በዓል የታቀደው ቅናሽም “እንደግዴታ የቀረበ” አለመሆኑን አብራርተዋል። ማህበሩ ያቀረበውን ጥያቄ ተከትሎ የተወሰኑ ሆቴሎች ቅናሹን “በፓኬጅ ማዘጋጀታቸውን” ማስታወቃቸውንም አክለዋል። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር)
🔴 ዝርዝሩን በጹሁፍ ማንበብ ይሄን ሊንክ ይጫኑ፦ ethiopiainsider.com/2024/14238/
-------------------------------------------------------------------------------------------
የ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ትኩስ ዜናዎችን እና ወቅታዊ ዘገባዎችን ለመከታተል፦
ድረ ገጽ ፦ ethiopiainsider.com​
ፌስቡክ ፦ ethiopiainsider
ትዊተር (ኤክስ) ፦ ethiopiainsider
ቴሌግራም፦ t.me/EthiopiaInsiderNews
ቲክቶክ፦ www.tiktok.com/@ethiopiainsider

Опубликовано:

 

1 окт 2024

Поделиться:

Ссылка:

Скачать:

Готовим ссылку...

Добавить в:

Мой плейлист
Посмотреть позже
Комментарии