በጎፋ ዞን ኬንቾ ሻቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት ምክንያት የደረሰውን አስከፊ አደጋ ተከትሎ በተወካዮች ምክር ቤት የታወጀው የሶስት ቀን ሃዘን ማብቃቱን በማስመልከት በሳውላ ከተማ የሻማ ማብራት ስነ ሰርዓት ተከናወነ
ሌሎችን ለማዳን ሲሉ ህይወታቸውን የሰውትን መዘከር ያለብን የተጎጂዎችን ቤተሰቦች በዘላቂነት በማቋቋም መሆን እንዳለበት የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ አሳስበዋል።
ርዕሰ መስተዳድሩ መላው ኢትዮጵያውያን ለተጎጂዎች እያደረጉት ላለው ድጋፍ አመስግነዋል ።
አከባቢው በቀጣይም የመሰል አደጋ ስጋት ሰላለበት በርከት ያለ ቁጥር ያለው የአከባቢው ነዋሪ ወደ ሌላ ቦታ ማዘዋዋር አስፈላጊ እንደሆነ አቶ ጥላሁን አንስተዋል። የማቋቋም ስራው ከፍተኛ ሃብት ስለሚጠይቅ
ቀጣይ የሚደረገው ድጋፍ ለቤት መስሪያ የሚውል ገንዘብና ቁሳቁስ ፤ የዕርሻ መሳሪያ ተጎጂዎች ቢለገሳቸው የሚል ጥሪ ርዕሰ መስተዳድሩ አስተላልፈዋል።
ዘጋቢ ፡ ሲሳይ ደበበ ነው
#ደሬቴድ #SouthRadioandTelevisionAgency #SNNPRS #Debub_Tv #South_Tv
በተጨማሪም የቪዲዮና ሌሎች መረጃዎቻችንን ለማግኘት የትክክለኛዎቹ አድራሻዎቻችን አባል በመሆን ይከታተሉ፡-
ፌስቡክ- / southradioandtelevisio...
ቴሌግራም - t.me/southRadi...
ዌብ ሳይት - www.srta.gov.et
ትዊተር - / southradioandtv
7 сен 2024