የኢትዮጵያ መንግስት ባለስልጣናት፤ በአማራ ክልል እየተፈጸመ የሚገኘውን “የዘፈቀደ የጅምላ እስር” በአፋጣኝ እንዲያቆሙ ዓለም አቀፉ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅት አምነስቲ ኢንተርናሽናል ጠየቀ። በክልሉ ባሉ ትልልቅ ከተሞች የመንግስት የጸጥታ ኃይሎች ካለፈው ቅዳሜ ጀምሮ እያካሄዱት ባለው ዘመቻ፤ በመቶዎች የሚቆጠሩ ሰዎች መታሰራቸውንም ተቋሙ አስታውቋል።
የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቱ ትላንት ማክሰኞ ምሽት ባወጣው መግለጫ፤ በሰሞኑ ዘመቻ ለእስራት ከተዳረጉት ሰዎች መካከል በክልሉ ባሉ የፌደራል ዩኒቨርሲቲዎች የሚያስተምሩ ምሁራን እንደሚገኙበት አመልክቷል። የዓይን እማኞች ለአምነስቲ ኢንተርናሽናል እንደተናገሩት፤ በአማራ ክልል የተለያዩ አካባቢዎች ያሉ ሲቪል ሰዎች የታሰሩት ባለስልጣናት ይዘው የመጡትን “የስም ዝርዝር” መሰረት በማድረግ ነው።
ሆኖም እነዚህ ባለስልጣናት የብርበራም ሆነ የእስር ትዕዛዝ እንዳላቀረቡ ድርጅቱ የዓይን እማኞችን ጠቅሶ በትላንቱ መግለጫው አስፍሯል። የተወሰኑት እስራት የተከናወኑት በምሽት እንደነበር እማኞቹ መግለጻቸውንም ድርጅቱ አክሏል። በእነዚህ እስራት ከፖሊስ አባላት ሌላ ወታደሮች ጭምር መሳተፋቸውንም የዓይን እማኞቹን ዋቢ አድርጎ ድርጅቱ ገልጿል።(ኢትዮጵያ ኢንሳይደር)
ተጨማሪውን ለማንበብ ይሄን ሊንክ ይጫኑ ethiopiainsider.com/2024/14242/
-------------------------------------------------------------------------------------------
የ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ትኩስ ዜናዎችን እና ወቅታዊ ዘገባዎችን ለመከታተል፦
ድረ ገጽ ፦ ethiopiainsider.com
ፌስቡክ ፦ ethiopiainsider
ትዊተር (ኤክስ) ፦ ethiopiainsider
ቴሌግራም፦ t.me/EthiopiaInsiderNews
ቲክቶክ፦ www.tiktok.com/@ethiopiainsider
2 окт 2024