ከግንቦት 12-14 በአዲስ አበባ ሰበካ በጎፋ አጥቢያ በተደረገው ታላቅ ጉባዔ ላይ የቀረበ ድንቅ ዝማሬ።
ሰብስክራይብ በማድረግ ወንጌልን ለዓለም እናድርስ!
ግጥም/Lyrics
ሰማይ ሊቀበልህ የተገባህ ጌታ
ለአንተ ነው ምስጋናዬ ለአንተ ነው | 2x|
የበረከት አምላክ የፍጥረት መዳኛ
ለአንተ ነው ዝማሬዬ ለአንተ ነው |2x|
ለክብርህ ከክብሬ ዝቅ ዝቅ ብዬ
ደግሞስ ተመርጬ የአንተ በመሆኔ
ዘምራለሁ ባለማዕረግ ነኝ
ድል የታወጀልኝ የንጉሥ ልጅ ነኝ
የክብር ንጉሥ ይግባ ኢየሱስ ይግባ እላለሁ
ቤቱን በእልልታ አሜን በእልልታ እሞላዋለሁ
የክብር ንጉሥ ይግባ ኢየሱስ ይግባ እላለሁ
ቤቱን ጭብጨባ አሜን ጭብጨባ እሞላዋለሁ
በራሱ ላይ ዘውድ የተጫነበት
አቤት ጽድቅ እና ታማኝነትህ
ቅዱስ ይሉታል እልፍ አእላፋት
በታላቅ ክብር ይጠሩታል
አመልከዋለሁ ጌታ ነው ጌታዬ
አነግሠዋለሁ ንጉሥ ነው ንጉሤ
በውበትህ በቅድስና
የምታስገርመኝ ገናና ሁሌም ገናና
ኃይልን ክብርን ዝናን ተላብሰህ
ያለህ እና የምትኖር አንተ ሁሌም ገናና
ልቤን በፊትህ አፈስሰዋለሁ
እንደ መላዕክት እዘምራለሁ
ክብርህ ያበራል |3x|
ጽድቅህም ስራህን ይናገራል
11 сен 2024