ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለሰው ልጆች ሁሉ የተቀበለውን መከራ መስቀል የኢትይጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን በመጽሃፍ ቅዱስ የተጻፈውን ዜማ ደርሳ እሴብህ ጸጋከ ዘመድሐኒአለም እያለች በኪዳኗ ሁሌ ታስበዋለች፡፡
ትንቢተ ኢሳይያስ 53፡4
4 ፤ በእውነት ደዌያችንን ተቀበለ ሕመማችንንም ተሸክሞአል፤ እኛ ግን እንደ ተመታ በእግዚአብሔርም እንደ ተቀሠፈ እንደ ተቸገረም ቈጠርነው።
5 ፤ እርሱ ግን ስለ መተላለፋችን ቈሰለ፥ ስለ በደላችንም ደቀቀ፤ የደኅንነታችንም ተግሣጽ በእርሱ ላይ ነበረ፥ በእርሱም ቍስል እኛ ተፈወስን።
6 ፤ እኛ ሁላችን እንደ በጎች ተቅበዝብዘን ጠፋን፤ ከእኛ እያንዳንዱ ወደ ገዛ መንገዱ አዘነበለ፤ እግዚአብሔርም የሁላችንን በደል በእርሱ ላይ አኖረ።
7 ፤ ተጨነቀ ተሣቀየም አፉንም አልከፈተም፤ ለመታረድ እንደሚነዳ ጠቦት፥ በሸላቶቹም ፊት ዝም እንደሚል በግ፥ እንዲሁ አፉን አልከፈተም።
20 апр 2024