Empress Taytu Betul Biography | የእቴጌ ጣይቱ አጭር የህይወት ታሪክ
#SUBSCRIBE# For More Similar Videos!
እቴጌ ጣይቱ ብጡል ብርሃን ዘኢትዮጵያ የዳግማዊ አፄ ምኒልክ ባለቤት እና በአደዋ ጦርነት ከነበሩ የጦር አዛዦች አንዷ ነበሩ:: እቴጌ ጣይቱ ከአባታቸው ከደጅአዝማች ብጡል እና ከእናታቸው ወይዘሮ የውብዳር እንደ ኢትዮጵያ አቆጣጠር በነሐሴ 12 ቀን 1832 ዓ.ም. ጐንደር ውስጥ በደብረ ታቦር ከተማ ተወለዱ:: የታሪክ ምንጮች እንደሚጠቁሙት ከሆነ እቴጌ ጣይቱ በአባታቸው ከጐንደር እና ከወሎ በእናታቸው ከጐጃም የሚወለዱ ሲሆን፣ በሀገራችን የነገሥታት ሚስቶች ታሪክ የራሳቸውን ዘመን ተሻጋሪ ፖለቲካዊ፣ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ ብሎም ወታደራዊ አሻራቸውን በደማቅ ጽፈው ያለፉ ብርቅ የኢትዮጲያ ንግሥት ናቸው።
22 окт 2024