በአቶ ጌታቸው ረዳ የሚመራው የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር፤ “የጥፋት ኃይል” ሲል የጠራው ቡድን የመንግስት “ግልበጣ አውጆብኛል” ሲል ከሰሰ። በዚህ ኃይል ላይ “ህጋዊ እርምጃ” እንደሚወስድ ያስታወቀው ጊዜያዊ አስተዳደሩ፤ በዚህ ሂደት ለሚፈጠር ማንኛውም አይነት ጥፋት “ብቸኛ ተጠያቂው”ይኸው ቡድን እና አመራሩ መሆኑን ገልጿል።
የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ይህን ያስታወቀው፤ ዛሬ ሰኞ መስከረም 27፤ 2017 ምሽት ባወጣው መግለጫ ነው። በትግራይ የኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ይፋዊ የፌስ ቡክ ገጽ ላይ የወጣው ይህ መግለጫ፤ የህወሓት አመራር “ለሁለት ከተሰነጠቀ በኋላ” የተከሰቱ ጉዳዮችን መለስ ብሎ ቃኝቷል።
ከነሐሴው አወዛጋቢ የህወሓት ጠቅላላ ጉባኤ በኋላ በአቶ ጌታቸው እና በዶ/ር ደብረጽዮን የሚመሩት የህወሓት ጎራዎች በየፊናቸው ህዝባዊ ስብሰባ ሲያካሄዱ እና ማስጠንቀቂያ ጭምር ያዘሉ የየራሳቸውን መግለጫዎች ሲያወጡ ቆይተዋል። በዶ/ር ደብረጽዮን የሚመራው የህወሓት ጎራ በዛሬ ዕለት ባወጣው መግለጫ፤ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት የሆኑት አቶ ጌታቸው ረዳን ከስልጣን ማንሳቱን አስታውቋል።
ይኸው ጎራ የጊዜያዊ አስተዳደሩ አራት የካቢኔ አባላትን ጨምሮ 13 አመራሮችን በተመሳሳይ መልኩ ከኃላፊነት ማውረዱን የገለጸ ሲሆን፤ በምትካቸውም ተተኪ የህወሓት ተወካዮችን መሾሙን ይፋ አድርጓል። የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ዛሬ ምሽት ባወጣው መግለጫ፤ “የቡድኑ” አካሄድ የመንግስት “ግልበጣ እወጃ” እንደሆነ ገልጿል።
🔴 ይህን ሊንክ ተጭነው ዝርዝር ዘገባውን ያንብቡ፦ ethiopiainside...
--------------------------------------------------------------------------------
የ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ትኩስ ዜናዎችን እና ወቅታዊ ዘገባዎችን ለመከታተል፦
ድረ ገጽ ፦ ethiopiainsider...
ፌስቡክ ፦ / ethiopiainsider
ትዊተር (ኤክስ) ፦ / ethiopiainsider
ቴሌግራም፦ t.me/EthiopiaI...
ቲክቶክ፦ / ethiopiainsider
7 окт 2024