#SUBSCRIBE # for more videos!
Artist Tesfaye Sahelu Biography
የዛሬው የታላቅ ነፍስ ዝግጅት ዕንግዳችን በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ላይ ስመጥርና የተወደዱ ተዋናይና በተለይም የሕፃናትና የልጆች ተረተኛ ናቸው። ለ42 ዓመታት በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ልጆችን ተረትና ምሳሌ በማስተማር፤ የሚታወቁት እና የኢትዮጵያ ልጆች አባት የሆኑት አንጋፋ የኪነ ጥበብ ሰው ናቸው። አቶ ተስፋዬ ሳህሉ ወይም ደግሞ በብዙኃን ዘንድ አባባ ተስፋዬ በመባል የሚታወቁት የኪነ ጥበብ ሰውን -- የልጅነት ጊዜውን በኢትዮጵያ ያሳለፈ ሁሉ ያውቃቸዋል ማለት ይቻላል። እኝህ ሰው በተረት መልክ በርካታ ኢትዮጵያንን ባህልን እና ቁም ነገርን አስተምረዋል። የእኝህን የብዙሃን አባት እና ታዋቂ የኪነ ጥበብ ሰው ማንነትና ስራቸውን በዛሬው ዝግጅታችን መለስ ብለን ቃኝተናል።
ቀናችን ልዩ የቅዳሜ ከሰዓት የመዝናኛ ሾው ዘውትር ቅዳሜ ከቀኑ 9፡00 - 11፡00 በዋልታ ኤፍ ኤም 105.3 ጣብያ፡፡ የአፍሪካ ፈርጥ፣ ልሳነ-ዜማ፣ ታላቅ ነፍስ፣ የጥበብ ስንቅ እና ሌሎች አዝናኝ እና አስተማሪ ፕሮግራሞችን በቀናችን ሳምንታዊ የመዝናኛ ሾው ያገኛሉ፡፡
7 ноя 2022