መጽሐፍ ቅዱስ የማይቀበላቸው ሚዛናቸውን ያዛቡ ሁለት ጫፎች (አክራሪ አቋሞች) አሉ። በመጀመሪያ፥ እግዚአብሔርን ለማስደሰትና ድነትን (ደኅንነትን) ለማግኘት አንዳች በጎ ተግባር መፈጸም አለብን የሚል አክራሪ አቋም አለ። በጳውሎስ ዘመን ለነበሩት አይሁዶች ይህ ማለት መገረዝ ወይም የብሉይ ኪዳን ሕግጋትን መጠበቅ ነበር። እነዚህ ሁሉ አመለካከቶች የዘላለምን ሕይወት ለማግኘት በክርስቶስ ማመንና ተጨማሪ ተግባራትን ማከናወን እንደሚያስፈልግ ያስረዳሉ። ሰዎች በወንጌሉ ላይ ሌሎች ነገሮችን የመጨመር ዝንባሌ አላቸው። በገላትያ መልእክት ውስጥ በወንጌል ትምህርት ላይ የሚጨምረው ትምህርት ተዳሷል። ሁለተኛ፥ የተወሰኑ እውነቶችና በክርስቶስ ላይ እምነት እስካለን ድረስ እንዳሻን ልንኖር እንችላለን የሚል ሌላ አክራሪ አቋም አለ። እነዚህ ሰዎች፣ እምነት እንዳሻን እንድንኖር ነፃ በማውጣት ያድነናል ይላሉ። ጳውሎስ ግን በእውነት ከዳንን እግዚአብሔርን በሚያስከብር መንገድ መመላለስ እንደሚገባን በአጽንዖት ያስገነዝባል።
12 сен 2024