ጉዞ ዓድዋ በአትላንታ
እንኳን ለ128ኛው የዓድዋ የድል በዓል በሰላም አደረሳችሁ!
ጉዞ ዓድዋ በአትላንታ ማህበር “ዓድዋ - የአንድነታችን የድል ውጤት” በሚል መሪ ቃል 128ኛው የዓድዋ የድል በዓል ለማክበር ዝግጅቱን አጠናቆ ይገኛል።
ቅዳሜ March 2,2024 ከጠዋቱ 7am ስድስተኛው ዙር ጉዞ ዓድዋ በስቶን ማውንቴን ተራራ! ኢትዮጵያውያን በህብረት ጠዋት ወደ ተራራው ግርጌ (ወረኢሉ) ተገናኝተን የዓድዋ ጦርነት መነሻ ታሪክ የውጫሌ ውል፤ የእቴጌ ጣይቱን የጦርነት አነቃቂ ንግግር፤የአፄ ሚኒሊክ የክተት አዋጅ ሰምተን በፉከራና በቀረረቶ ታጅበን ተራራውን እንወጣለን፤ በጉዞ ላይ ስለ አምባላጌው፤ስለ መቀሌው ጦርነት፤በመጨረሻም ወደ ተራራው ጫፍ ዓድዋ በመድረስ ታሪኩን እንማራለን፤ጀግኖቻችን እንዘክራለን፤ሰንደቃላማችን እናውለበልባለን። ታሪካችን ለልጆቻችን እናስተላልፋለን።
በመጨረሻም ንጉሶቻችን ክብራቸውን በሚመጥን መልኩ ከStone mountain እስከ Decatur ክፍት በሆነ መኪና በባንዲራችን አጀበን በአይቤክስ ሬስቶራንት በተዘጋጀው የሚኒሊክ የግብር አዳራሽ ምግቡን እና መጠጡን አዘጋጅተን፤በትወና እና በተለያየዩ ዝግጅቶች ዓድዋችን ደመቅመቅ እናደርገዋለን።
ፕሮግራሙ ላይ ለመሳተፍ እና ቲሸርት ለማግኘት guzoadwaatlant... ተመዝገቡ።
የዓድዋ ድል ከኢትዮጵያዊውያን አልፎ የመላው የጥቁር ህዝቦች ሁሉ ድል ነው። ለበለጠ መረጃ አስተባባሪዎቹን
በ 770 256 4060፣ 404 247 7667፣ 404 394 9321 ይደውሉ።
ዓድዋ - የአንድነታችን የድል ውጤት
21 окт 2024