ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ በመሬት ናዳ 257 ዜጎች የሞቱበትን፤ የጎፋ ዞን ኬንቾ ሻቻ ጎዝዲ ቀበሌን በአካል በመገኘት ተመለከቱ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ወደ ቦታው የተጓዙት አደጋው በደረሰ በስድስተኛው ቀን ነው።
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል፤ ኬንቾ ሻቻ ጎዝዲ ቀበሌ ሰኞ ሐምሌ 15፤ 2016 በደረሰው ድንገተኛ የመሬት መንሸራተት አደጋ ህይወታቸውን ካጡ ሰዎች መካከል አስክሬናቸው የተገኙ ሰዎች ቁጥር 226 መሆኑን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ኮሚዩኒኬሽን ቢሮ ትላንት ምሽት አስታውቋል። የአስክሬን ፍለጋው ተጠናክሮ መቀጠሉን ገልጿል።
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰብዓዊ ጉዳዮች ማስተባበሪያ ጽህፈት ቤት በበኩሉ፤ የሟቾቹ ቁጥር ወደ 257 ማሻቀቡን እና አጠቃላይ የአደጋው ሰለባዎች ቁጥር 500 ሊደርስ እንደሚችል ከትላንት በስቲያ ባወጣው ሪፖርት አመልክቷል። ጽህፈት ቤቱ ለተጨማሪ የመሬት መንሸራተት አደጋ በከፍተኛ ሁኔታ ሊጋለጡ የሚችሉ 15,515 ነዋሪዎች በአፋጣኝ ከአካባቢው እንዲለቅቁ ሊደረግ እንደሚገባም በሪፖርቱ አሳስቦ ነበር።(ኢትዮጵያ ኢንሳይደር)
ተጨማሪውን ለማንበብ ይሄን ሊንክ ይጫኑ ethiopiainside...
-------------------------------------------------------------------------------------------
የ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ትኩስ ዜናዎችን እና ወቅታዊ ዘገባዎችን ለመከታተል፦
ድረ ገጽ ፦ ethiopiainsider...
ፌስቡክ ፦ / ethiopiainsider
ትዊተር (ኤክስ) ፦ / ethiopiainsider
ቴሌግራም፦ t.me/EthiopiaI...
ቲክቶክ፦ / ethiopiainsider
17 окт 2024