#mezmur #አዲስ_ዝማሬ #mezmurorthodox
🆂🆄🅱🆂🅲🆁🅸🅱🅴
ሰው ሰውን በንግግሩ ያደማል
እግዚአብሔር በዝምታ ያክማል
እኛ በአደባባይ በግፍ በፈረድነው
በጓዳ እያከመ ስንቱን ሰው አቆመው
የጻድቃን ከንፈሮች ደስታን ይሰጣሉ
ኃጥአን በክፉ ቃል አንገት ያስደፋሉ
ደከመ ብላችሁ በዚያ ሰው ስትፈርዱ
ተፈላጊ እርሱ ነው ያ የጠፋው አንዱ
የሸንጋይ ሰው እድሜ ግማሽም አይሞላ
እንደ ይሁዳ ነው ፍጻሜው በኋላ
ግዙፉን የዘመኑን እርቃን አካል
ምላስን ማራቆቱ መች ይበጃል
ከያዕቆብ ጉድጓድ በቀትር መምጣቴ
ከሰዎች ምላስ ነው ሽሽት እና እፍረቴ
ከውሃው ብቻ አይደል እኔስ መጠማቴ
ሰው የራበኝ ሰው ነኝ ታውቃለህ አባቴ
ሀገሩን አቋርጠህ ሰፈሬ ባትመጣ
እድሜዬ ያልቅ ነበር ከቤቴ ሳልወጣ
የቅርቤ አስታዋሼ እልሃለው
ሰው ባጣ ሰው ለሆንከኝ እዘምራለሁ
ሩቅ አልነበረም ወንዙ ለአልጋው
ገፋ እንኳን ቢያደርጉት ከመጠመቂያው
ያ ሁሉ ሰው ሲሄድ ድኖ ሲመለስ
አንድም አልተገኘም እርሱን ሚያስታውስ
መጻጉዕ እየጮኸ እርዱኝ ቢል ተኝቶ
አትጩህ ሚለው በዛ የሚረዳው ታጥቶ
በከንቱ ያለምክንያት ቢጠሉን
አለልን ያለምክንያት ሚወደን
ጌታ ካቀለጠው የበደልን መዝገብ
ሰው ለምን ይደክማል የድሮን በማንበብ
መንግሥቱ የጽድቅ ነው ለሁሉ የሚበቃ
ተቆርቋሪ አይሻም የሚኮንን ጠበቃ
እንደዚህ ነበረች እንዲያ ነው አትበሉ
ለሁሉም እኩል ነው ፍቅር ነው አመሉ
ግዙፉን የዘመኑን እርቃን አካል
ምላስን ማራቆቱ መች ይበጃል
ከመንገድ ተጥዬ ሁሉም እያለፈኝ
አንድ አንተ አይደለህ ወይ አይተህ ያላለፍከኝ
ምን አለ ዝም ቢሉ እገዛው ቀርቶብኝ
ከቆሰልኩት በላይ ነው ቃላቸው አመመኝ
ስንቱን ሰው ታዘብኩት እኔማ ተኜቼ
ሚያልፈኝ በበዛበት ሚያይ አንተን አይቼ
ውድቀቴን ባየሁበት በዚያው ቦታ
ካንተ ጋር ቆሜ ታየሁ በከፍታ
ግጥም: ዘማሪ ኢንጂነር ታዴዎስ አውግቸው
ዜማ: አንተነህ ተክለማርያም
____________/Connect With Me On Social Media\____________
► Telegram:➜@ramapost/ #0928311773
► Tiktok:➜@tadewos7
► Facebook:➜ / rama-tube-ll. .
► Instagram:➜@tadewosawugchew
==========================
Please follow my channel guidelines when you join the conversation.
1.On this channel you agree to be civil and respectful.
2.You understand questions are welcomed,but not spammed.
3.You understand to stick to the topic of the
25 мар 2024