ሐሰተኞች ሲገለጡ ይወራጫሉ፤ ይበሳጫሉ፤ ይወናጨፋሉ፤ ይናደፋሉ። ('ሐዋርያ' ይዲድያ ጳውሎስ።)
ሐሰተኛ ነቢያትን አሁን ሕዝባውያንና ማኅበራውያን ጋዜጠኞችም በጢስ እያፈኗቸው ናቸው። እነርሱም እየተወራጩ ናቸው። ሐሰተኞች ሲገለጡ ወገቡን እንደተመታ እባብ ናቸው። እባቡ እንዲያ ከተመታ ለመሸሽም፥ ለመናደፍም የሚችለውንም የማይችለውንም ያደርጋል።
ሐሰተኛ ነቢያትና ሐሰተኛ ሐዋርያትም ሐሰተኝነታቸው ሲገለጥ እጅግ በጣም ይወራጫሉ፤ ይበሳጫሉ፤ ይወናጨፋሉ፤ ይላከፋሉ፤ ይናደፋሉ፤ ይናከሳሉ፤ ይሳደባሉ።
እባብ አዲስ ቁርበት ሲያበቅል አሮጌውን ቆዳውን ይገፍፋል፤ ጊንጦችም exoskeleton የሚባል ውጪያዊ ቆዳ ወይም ቅርፊት አላቸው። እባብ ቆዳውን ሲገፍፍ ወይም ጊንጥ ከአሮጌ ቅርፊት ሲወጣ በጣም ስስ ገላ ስለሚኖራቸው ለአደጋ በጣም ይጋለጣሉ። ትናንሿ የምትነካቸው ነገር ትቆጠቁጣቸዋለች፤ ታሳምማቸዋለች። ስለዚህ ወይ አዲሱ ቆዳቸው እስኪደድር ድረስ ይሰወራሉ፤ ይደበቃሉ ወይም በነካቸው ነገር ሁሉ እየተሰቃዩ ይወራጫሉ።
ለናሙና አንዱን እንየው፤ ሀብታሙ ጳውሎስ ይባላል።
27 авг 2024