20 አመታትን በሩጫ ለዛውም በትላልቅ ድሎች በደስታ ሲያስለቅሱን ከነበሩት አንዷ የነበረችው የኢትዮጵያ ጌጥ አትሌት ኮማንደር ጌጤ ዋሚ ያው ከሩጫው አለም ከወጣች 14 አመታትን አስቆጥራለች፡፡ አሁን ደብረብርሀን ላይ ሆቴል በመክፈት ለ200 ሰዎች የስራ እድል መፍጠር ችላለች፡፡
• ስለ ልጄ እያሰብኩ ስሮጥ ክፉኛ ወድ...
በእኛ ጊዜ ሁሌም አንድ ላይ ነበር የምንሰራው ብሄራዊ ቡድን ስለነበረን ፍቅር ፣ አብሮ መስራት ፣ መተባበር ፣ መቀራረብ እና መተዛዘኑ ልዩ ይመስለኛል ትላለች ኮማንደር አትሌት ጌጤ ዋሚ ሲዲኒ 10000 ያሸነፍንበት መቼም አልረሳውም፡፡ በርሊን እሮጬ በ35 ቀናት ልዩነት ኒውዮርክ ላይ ሁለተኛ መውጣቴ ያስደስተኛል፡፡ ከፍተኛ የገንዘብ ሽልማት ያገኘሁትም 500ሺ ዶላር ነበር፡፡
አሰልጣኛችን ዶ/ር ወልደመስቀል ኮስትሬ ለእኛ ተሰውተዋል ብዙ ዋጋ ከፍለውልናል፡፡
ወልደን እንደ እናት ሳንታረስ ከለሊቱ በ9 ሰዓት ከጅብ ጋር እየተጋፋን ሰርተናል ግን ድልም ቀንቶን ነበር፡፡
የህይወት ጉዞዋንና የሩጫ ህይወቷን የኢትዮጵያ ጌጥ በተሰኘው መፅሀፍዋ ለተተኪ ትውልድ ብዙ ብላለች፡፡
አዝናኝ እና ቁምነገር አዘል ቪዲዮዎችን በየሳምንቱ ለመመልከት Seifu on EBS bit.ly/2VgLrdM Subscribe በማድረግ ደንበኛችን ይሁኑ
Subscribe
Seifu ON EBS - bit.ly/2VgLrdM
#SeifuFantahun #SeifuonEBS #SeifuFantahunShow
1 окт 2024