Тёмный
No video :(

ስለ ሥላሴ የሚናገሩ የመጽሓፍ ቅዱስ ክፍሎች || Paster Asfaw Bekele 

እውነት ያሳርፋል Ewnet Yasarfal
Подписаться 29 тыс.
Просмотров 3,7 тыс.
50% 1

You can use this link to get the original video.‌‌
• የምታምነውን እወቅ | ትምህርተ ስላ...
መልካም ዜና
የምስራች፣ የምስራች፣ የምስራች! የምስራች ማለት መልካም ዜና ማለት ነው። የእግዚአብሔር ቃል ደጋግሞ የሚነግረን ይሄ መልካም ዜና ምንድነው? ዛሬ፣ በእግዚአብሔር ረዳትነት፣ በእግዚአብሔር ቃል ላይ ስለተጠቀሰው ስለዚህ መልካም ዜና እንነጋገራለን። ነገር ግን ስለ መልካሙ ዜና ከመነጋገራች በፊት ስለ መጥፎው ዜና ማስታወስ አለብን።
ምንድነው መጥፎው ዜና? በመጀመሪያ እግዚአብሔር ሰማይንና ምድርን ከፈጠረ በኋላ አዳምንና ሔዋንን በምድራዊዋ ገነት ውስጥ እንዳስቀመጣቸው ታስታውሳላችሁ። እግዚአብሄር እንዲያውቁት፣ እንዲወዱት፣ እንዲታዘዙት እና ለዘላለም እንዲያከብሩት ፈጥሯቸዋል። ይሁን እንጂ እግዚአብሔር እነሱን ለመፈተን አዳምን እንዲህ አለው፡-
“በገነት ካለው ከዛፉ ፍሬ ብሉ፥ ነገር ግን እንዳትሞቱ በገነት መካከል ካለው ከዛፉ ፍሬ አትብሉ አትንኩትም።”
መጥፎው ዜና አዳምና ሔዋን እባቡን ማለትም ከተከለከለው ዛፍ ፍሬ እንዲበሉ የፈተናቸውን ዲያብሎስን ማዳመጣቸው ነው። የአዳምና የሔዋን ኃጢአት እነርሱንና ዘሮቻቸውን ሁሉ በመበከል በዓለም ላይ ችግርንና ሞትን አመጣ። ብዙ ጊዜ እንደምንሰማው፡ "ወረርሽኝ መነሻው ላይ ብቻ አይወሰንም!" የእግዚአብሔር ቃል እንዲህ ሲል መጥፎ ዜና ይነግረናል፡-
“ለሰዎችም አንድ ጊዜ መሞት ከእርሱ በኋላም ፍርድ እንደ ተመደበባቸው፥...
እነሆ፥ ጌታ በሁሉ ላይ እንዲፈርድ፥ በኃጢአተኝነትም ስላደረጉት ስለ ኃጢአተኛ ሥራቸው ሁሉ ዓመፀኞችም ኃጢአተኞች በእርሱ ላይ ስለ ተናገሩ ስለ ጭከና ነገር ሁሉ ኃጢአተኞችን ሁሉ እንዲወቅስ ከአእላፋት ቅዱሳኑ ጋር መጥቶአል ብሎ ለእነዚህ ደግሞ ትንቢት ተናገረ።” (ዕብራውያን 9፥27 ይሁዳ 1፥15)
ስለዚህ፣ መጥፎው ዜና ሁላችንም ኃጢአተኞች ነን እናም የእግዚአብሔርን የጽድቅ ፍርድ መጋፈጥ አለብን! ይሁን እንጂ፣ መልካሙ ዜና (የምስራቹ) በዚያው በገነት ውስጥ፣ በምረቱ ባለጠጋ የሆነው እግዚአብሔር፣ አንድ ቀን ከድንግል የሚወለድን ኃጢአት የሌለበትን ሰው ወደ አለም እንደሚልክ ማስታወቁ ነው። ይህ ቅዱስ ሰው፣ ይህ ጻድቅ አዳኝ፣ ለአዳምና ለዘሮቹ ሁሉ ኃጢአት ለመክፈል ራሱን መስዋእት አድርጎ ይሞት ነበር። ለኛ የሚገባን የኃጢአት ቅጣት በዚህ ኃጢአት በሌለበት አዳኝ ላይ ይወድቃል። አዳምና ሔዋን ኃጢአት በሠሩበት ቀን እግዚአብሔር የሰበከው ወንጌል (የምስራች) ይህ ነው። እግዚአብሔር የዚህን አዳኝ መምጣት ለማወጅ ብዙ ሰዎችን ተጠቅሟል፣ እንዲሁም መሲህ ይባላል። እያንዳንዱ የእግዚአብሔር ነቢያት ስለ መሲሑ አንድ ነገር አውጀዋል፣ ስለዚህም እርሱ ሲመጣ እግዚአብሔር የሾመው እርሱ መሆኑን ሁሉም ይገነዘባል። ለምሳሌ ያህል፣ ከመሲሑ መምጣት ሰባት መቶ ዓመታት ቀደም ብሎ የነበረው ነቢዩ ኢሳይያስ፣ መሲሑ እንዴት እንደሚወለድ ተንብዮአል። "ድንግል ትፀንሳለች ወንድ ልጅም ትወልዳለች ስሙንም አማኑኤል ብላ ትጠራዋለች ትርጓሜውም እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ማለት ነው።"( ማቴ. 1:23፤ ኢሳ. 7:14 ) ሚክያስ የተባለ ነቢይ ደግሞ መሲሁ ከሰማይ መጥቶ በቤተልሄም መንደር በምድር ላይ እንደሚወለድ ትንቢት ተናግሯል። በትክክል መሲሑ የተወለደበት ቦታ ይህ ነበር። ሆኖም ሚክያስ ይህን ትንቢት የተናገረው መሲሑ ከመወለዱ ከብዙ መቶ ዓመታት በፊት ነው። ነገር ግን ነቢያት የመሲሑን መወለድ ብቻ አላወጁም። በተጨማሪም መሲሁ በኃጢአተኞች ምትክ መከራ እንደሚደርስበትና እንደሚምት ትንቢት ተናግረዋል። ለምሳሌ ነቢዩ ዳዊት ሰዎች መሲሑን እንደሚንቁት፣ እንደሚያሰቃዩት፣ እጁንና እግሩን እንደሚወጉ እና እንደሚገድሉት ጽፏል። ዳዊት የመሲሑን ሞት ማወጅ ብቻ ሳይሆን፣ እግዚአብሔር መሲሁን ከሞት እንደሚያስነሳውም ተንብዮአል፤ ይህም እግዚአብሔር የአዳምን ልጆች ከኃጢአት ቅጣት ለማዳን የላከው አንድና ብቸኛ አዳኝ መሆኑን አረጋግጣል።
ስለ መሲሁ መወለድ ብዙም ክርክር የለም፣ ነገር ግን ብዙዎች በሞቱና በትንሳኤው ይሰናከላሉ። ሰዎች የላከውን መሲህ ሲያዋርዱት እግዚአብሔር እንዴት ሊቆም እና ሊመለከት እንደሚችል አይገባቸውም። ብዙ ሰዎች ሊረዱት ያልቻሉት ነገር መሲሑ ለኃጢአታችን እንዲህ አይነት መከራ እንዲደርስበት ያቀደው እኛን የሚወደን አምላክ መሆኑን ነው። ነገር ግን ነቢያቱ እንዲህ ሲሉ አውጀዋል፡- “እግዚአብሔርም በደዌ ያደቅቀው ዘንድ ፈቀደ፤ ነፍሱን ስለ ኃጢአት መሥዋዕት ካደረገ በኋላ ዘሩን ያያል፥ ዕድሜውም ይረዝማል፥ የእግዚአብሔርም ፈቃድ በእጁ ይከናወናል።”
- (ኢሳይያስ 53፥10)
ነቢያትን እናምናለን? አዎ እናምናቸዋለን እንላለን። ነቢያትን በእርግጥ የምናምን ከሆነ የጻፉትንም ማመን አለብን። ነብያት የራሳቸውን ሃሳብ እንዳልተናገሩ ማስታወስ አለብን። እግዚአብሔር የሚናገሩትን በመንፈሳቸው ውስጥ አኖረ። እንግዲያውስ እነዚያን ነቢያት ለማመን ብንቃወም፣ ማንን ነው ምንቃወመው? የምንቃወመው እግዚአብሔርን ነው። ምክንያቱም ነቢያት መሲሁ ኃጢአትን ለማስወገድ መስዋዕት ሆኖ እንደሚሞት ትንቢት እንዲተነብዩ ያነሳሳው እርሱ ነውና።
{የሚቀጥለው ማሊክ የሚባል ሰው የግል ምስክርነት ነው።} እዚህ ጋር ቆም ላድርገውና እንዴት በኢየሱስ ክርስቶስ አማኝ እንደሆንኩ ልንገራችሁ። በወጣትነቴ በቀን አምስት ጊዜ ለመጸለይ እና አመታዊ ጾምን ለመጾም ታማኝ ነበርኩ፣ ነገር ግን ከሞትኩ በኋላ ወዴት እንደምሄድ አላውቅም ነበር። ዙሪያዬ ያሉትን ሁሉ ጠየኩ፣ ሆኖም ግልጽ የሆነ መልስ አላገኘሁም። ወንጌልን (ኢንጂልን) ሳጠና ግን፣ ከሞቴ በኋላ ወዴት እንደምሄድ ማወቅ እንደምችል አወቅሁ፤ ምክንያቱም መሲሁ ኢየሱስ ራሱ በወንጌል እንዲህ ይላል፦ “እውነት እውነት እላችኋለሁ፥ ቃሌን የሚሰማ የላከኝንም የሚያምን የዘላለም ሕይወት አለው፥ ከሞትም ወደ ሕይወት ተሻገረ እንጂ ወደ ፍርድ አይመጣም።” (ዮሐንስ 5፥24) እንዲሁም እንዲህ ብሏል፦ “ኢየሱስም፦ ትንሣኤና ሕይወት እኔ ነኝ፤ የሚያምንብኝ ቢሞት እንኳ ሕያው ይሆናል፤” (ዮሐንስ 11፥25) ስለዚ፣ ራሴን ለማዳን ከራሴ ጥረት ንስሃ ገብቼ ነቢያት ሁሉ “በእርሱ የሚያምን ሁሉ በስሙ የኃጢአቱን ስርየት ይቀበላል" ብለው ትንቢት በተናገሩለት መሲህ አመንኩኝ (ሐዋርያት 10፥43)። ተስፋዬን ሁሉ ወስጄ በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ ላይ አስቀመጥኩት። ከዚያን ጊዜ ጀምሮ እስከ አሁን ድረስ እግዚአብሔር ለመንፈሴ ሰላም አምጥቶላታል። አሁን ህሊናዬ አይረበሽም። ኢየሱስ በመስቀል ላይ ከሰራው ሥራ የተነሳ የወደፊት እጣዬ በሚያስደንቅ ሁኔታ ብሩህ ነው። በሕይወቴ እንደ ክርስቶስ ደቀ መዝሙር፣ አንዳንድ ጊዜ ችግር እና መከራ ያጋጥመኛል ምክንያቱም እምነቴ ከዘመዶቼ እና ከጓደኞቼ አስተያየት ስለሚለያይ፤ ግን ሰላም አለኝ። የእግዚአብሔር ሰላም ልቤንና አእምሮዬን ሞልቶታል። ይህን የሰጠኝ ኢየሱስም እንዲህ ይላል፦ “ዓለም ቢጠላችሁ ከእናንተ በፊት እኔን እንደ ጠላኝ እወቁ።” (ዮሐንስ 15፥18) “ሰላምን እተውላችኋለሁ፥ ሰላሜን እሰጣችኋለሁ፤ እኔ የምሰጣችሁ ዓለም እንደሚሰጥ አይደለም። ልባችሁ አይታወክ አይፍራም።” (ዮሐንስ 14፥27) እና ወዳጆች ሆይ፣ ጌታ ለእኔ እና በእኔ ያደረገውን ለእያንዳንዳችሁ ሊያደርግ ይችላል። ካንተ ወይም ካንቺ አንድ ነገር ይጠይቃል፡-ሙሉ ልብህን እንድትሰጠው። ሙሉ ልብሽን እንድትሰጪው። የቀረውን እሱ ያደርገዋል። ጌታ ኢየሱስ ራሱ እንዲህ ብሏልና። "እናንተ ደካሞች ሸክማችሁ የከበደ ሁሉ፥ ወደ እኔ ኑ፥ እኔም አሳርፋችኋለሁ። ቀንበሬን በላያችሁ ተሸከሙ ከእኔም ተማሩ፥ እኔ የዋህ በልቤም ትሑት ነኝና፥ ለነፍሳችሁም ዕረፍት ታገኛላችሁ፤" (ማቴ. 11:28-29)
እግዚአብሔር ታላቁን ማዳኑን መቼም ቢሆን አይሸጥልህም ወይም አይሸጥልሽም። እንዲሁ ያለ ምንም ዋጋ (ከእናንተ ባልሆነ ዋጋ) በነጻ ሊሰጣችሁ ነው ሚፈልገው። መልካም ስራ፣ ፀሎት (ሶላት) እና ፆም በውስጣችሁ ጥሩ ስሜት ይሰጡ ይሆናል፣ ነገር ግን የእግዚአብሔርን ፅድቅ አያረኩም! ወደ እግዚአብሔር ገነት የምትገባበት/የምትገቢበት መንገድ አንድ ብቻ ነው።
1.) በመጀመሪያ ኃጢአተኛ እንደሆንክና አምላክን ለማስደሰት የሚያስችል ኃይል እንደሌለህ መገንዘብ ይኖርብሃል።
2.) ከዚያም ኢየሱስ ክርስቶስ አዳኝ እንደሆነ፣ ኃጢአትህን ለማስወገድ እግዚአብሔር በመስቀል ላይ እንዲሞት እንደ ላከውና እግዚአብሔር የዘለአለም ሕይወትን ይሰጥህ ዘንድ እንዳስነሳው ማመን አለብህ።
የኦሮምኛውን ቻናሌን ለማግኘት ይህንን ተጫኑ👇
/ @dhugaanniboqachiisa
አስተያየታችሁን በውስጥ ማድረስ የምትፈልጉ ይህንን የቴሌግራም ሊንክ ተጠቀሙ👇
t.me/BibleAndMe
Additional: - ewnetyasarfal123@gmail.com

Опубликовано:

 

23 авг 2024

Поделиться:

Ссылка:

Скачать:

Готовим ссылку...

Добавить в:

Мой плейлист
Посмотреть позже
Комментарии : 30   
@15Abel
@15Abel 27 дней назад
እግዚአብሔር ይባረካቸው ቶሎ ቶሎ ❤❤❤❤ ሊቀቁ እና ከእናንተ ብዙ እየተማረኩ እግዚአብሔር ዘመናችሁን የባርኪና እናንተን ይደግታቸው ተባረኩልኝ
@Tinay-l5h
@Tinay-l5h 22 дня назад
ይህን የገለጠሎት እግዚአብሔር አምላክ በጌታ በኢየሱስም ለዘላለም የተ ባረካ ይሁን ዋውው
@samuelsahle3295
@samuelsahle3295 2 месяца назад
ትልቅ መረዳት ነው ጌታ አሁንም ይግለጥልህ
@user-cl8wm7rj8b
@user-cl8wm7rj8b Месяц назад
ጌታ ይባርክሕ !!
@gessemmedia4116
@gessemmedia4116 12 дней назад
መደንዘዝ ካልቀረ የሥላሴ ሰባኪ አትሁኑ
@user-uy2qu6py6n
@user-uy2qu6py6n 2 месяца назад
እኔ ኦርቶዳክስ ነኝ ከፖስተር ስለ ስላሴ እንዲ ያለ መረዳት የገለፀልህ እግዚአብሔር ይመስገን ስለ ቅድሳንም ያለህን መረዳት ብናውቅ ጥሩ ነው እግዚአብሔር አሁንም እውነትን እዲገልፅልህ እንፀልያለን።
@TammyTammy-mt9wu
@TammyTammy-mt9wu 2 дня назад
Wawu.Libe Kin Nek❤❤❤
@user-kq5wi2tt4n
@user-kq5wi2tt4n Месяц назад
ጌታ ይባርክህ, ጴጥሮስ ባጠመቃቸው only jesus church የሚሉ በዛ ላይ እየተሳሰቱ ነው በዛ ላይ ስራ
@hywate
@hywate 3 месяца назад
እውነት ነው ተባረክልን ፓስተር 🙏🙏 እግዚአብሔር አሁንም ጸጋውን ይጨምርልህ🙏🙏🙏
@eigtyk82ghir
@eigtyk82ghir 3 месяца назад
ተባረክ ወድም ጎበዝ በርታ እዲህ ህዝቡ ይቃ ተባረክ ፓስተር ጸጋይጨመርሎት❤
@TammyTammy-mt9wu
@TammyTammy-mt9wu 2 дня назад
Silase Beker Lela Amilak Hulu.Taotinewu Sost Akal.Andi.Amilak Yene Amilak
@tenagnefiseha1143
@tenagnefiseha1143 3 месяца назад
አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ ስላሴ መለት ነው ወይም አምላክ የንድም ሶስትም መለት ነው
@gessemmedia4116
@gessemmedia4116 12 дней назад
ሦስቱን ደምረን አንድ አንዱንም ደምረን ሦስት አይሆንም መደንዘዝ ካልሆነ
@mintesnot6857
@mintesnot6857 6 месяцев назад
ማቴዎስ 28 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹⁸ ኢየሱስም ቀረበና እንዲህ ብሎ ተናገራቸው፦ ሥልጣን ሁሉ በሰማይና በምድር ተሰጠኝ። ¹⁹-²⁰ እንግዲህ ሂዱና አሕዛብን ሁሉ በአብ በወልድና በመንፈስ ቅዱስ ስም እያጠመቃችኋቸው፥ ያዘዝኋችሁንም ሁሉ እንዲጠብቁ እያስተማራችኋቸው ደቀ መዛሙርት አድርጓቸው፤ እነሆም እኔ እስከ ዓለም ፍጻሜ ድረስ ሁልጊዜ ከእናንተ ጋር ነኝ።
@ewnetyasarfal
@ewnetyasarfal 6 месяцев назад
🥰🥰🥰
@marveltech521
@marveltech521 2 месяца назад
“መዳንም በሌላ በማንም የለም፤ እንድንበት ዘንድ የሚገባን ለሰዎች የተሰጠ ስም ከሰማይ በታች ሌላ የለምና።” - ሐዋርያት 4፥12 “ነገር ግን እላለሁ፥ ወራሹ ሕፃን ሆኖ ባለበት ዘመን ሁሉ፥ ምንም የሁሉ ጌታ ቢሆን ከቶ ከባሪያ አይለይም፥” - ገላትያ 4፥1 ዕብራውያን 1 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ² ሁሉን ወራሽ ባደረገው ደግሞም ዓለማትን በፈጠረበት በልጁ በዚህ ዘመን መጨረሻ ለእኛ ተናገረን፤ … ⁴ ከመላእክት ይልቅ እጅግ የሚበልጥ ስምን በወረሰ መጠን እንዲሁ ከእነርሱ አብዝቶ ይበልጣል። ፊልጵስዩስ 2 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ⁹ በዚህ ምክንያት ደግሞ እግዚአብሔር ያለ ልክ ከፍ ከፍ አደረገው፥ ከስምም ሁሉ በላይ ያለውን ስም ሰጠው፤ ¹⁰ ይህም በሰማይና በምድር ከምድርም በታች ያሉት ሁሉ በኢየሱስ ስም ይንበረከኩ ዘንድ፥ ¹¹ መላስም ሁሉ ለእግዚአብሔር አብ ክብር ኢየሱስ ክርስቶስ ጌታ እንደ ሆነ ይመሰክር ዘንድ ነው። ኢሳይያስ 64 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹ ሰማዮችን ቀድደህ ምነው ብትወርድ! ተራሮችም ምነው ቢናወጡ! ² እሳት ጭራሮውን እንደሚያቃጥል፥ እሳትም ውኃውን እንደሚያፈላ፥ ስምህ ለጠላቶችህ ይገለጥ ዘንድ፥ አሕዛብም በፊትህ ይንቀጠቀጡ ዘንድ። ኢየሱስ የአብ ስም ነው
@AsterEr
@AsterEr 25 дней назад
ጥያቄ ፦ ተዋህዶ ማለት ምን ማለት ነዉ? በሰማይ ላይ ይመካከሩ ነበር ላሉት ስንት ነቸው ? በቁጡርስ ስንት ብለዉ ቁጥር ይሰጡታል ? አንድም ሶስትም? ወይስ አርባ አራት ? አሁንስ ከዚህም በላይ እየሆኑባችሁ አይደለም ወይ? እኔ ብቻዬን ንኝ ያለዉ አምላክ ፦ በኢሳይያስ መጽሐፍ ም43;45;46; ኤር ም 10; ራዕይ ም22 ላይ ያለዉ ቃል አይፈርድባችሁም ወይ? በአንድ አምላክ ላይ ሌሎችን መጨመር እኮ ጣዖታትን ማምለክ ነዉ ይላል ቃሉ ። በጥቂቱ ከላይ በተዘረዘሩ ቃሎች ፦ እንዴይፈረዲባችሁ አስቡበት እላለሁ ። እኔስ ፦ብቻን አምላክ ፤ አባትና የዘላለም ሕይወት ፤ የሆነዉን በስሙ ጥምቀት ለብሸዉ ከመርገም ወደ ዘላለም ሕይወት ያሻገረኝ፦ አንድ አምላክ ስሙ ኢየሱስ ለዘላለም ይመስገን!!! ሃሌሉያ።
@ruthabera72
@ruthabera72 5 месяцев назад
Glory be to God thanks for!sharing
@user-xt1jk4dm6h
@user-xt1jk4dm6h 3 месяца назад
ግን እናንተ መናፍቃን ናቹ ወይ ተዋህዶ?
@ewnetyasarfal
@ewnetyasarfal 3 месяца назад
ከትምህርቱ ምን ተረዳህ? መናፍቅ እንደሆነ ወይስ እንዳልሆነ? ክርስቲያን ከሆንክ ከእንደዚህ አይነት ከንቱ ንግግር ውጣና የእግዚአብሔርን ቃል አንብብ፣ እንደ እግዚአብሔር ቃል ተናገር፣ መስክር ፣ እንደ እግዚአብሔር ቃል ሞግት። መናፍቅ ናችሁ ወይስ ተዋህዶ🤮🤧
@saronisrael752
@saronisrael752 3 месяца назад
ትልቅ ጥያቄ ነው ትርጉሙ ተመችቶኛል መጨረሻውን እናያለን
@ElduErsumo
@ElduErsumo Месяц назад
Inga manafki aydelenim christan neni anchi satongi akerim manafki ok
@ElduErsumo
@ElduErsumo Месяц назад
​@@saronisrael752miskini
@masara7252
@masara7252 6 месяцев назад
Egezehabeher amelk yebarakachu ❤❤❤❤
@mintesnot6857
@mintesnot6857 6 месяцев назад
Hallelujah🥰🥰🥰
@AmbachewuAssefa-sn2iw
@AmbachewuAssefa-sn2iw 4 месяца назад
የሚገርም ግልፅ የሆነ ትንተና
@gessemmedia4116
@gessemmedia4116 12 дней назад
ኢየሱስን ልጅ ነው የሚል ሁሉ የማርያም ልጅ ነው ኢየሱስ የማርያም ልጅ አይደለም
@tagesseassefa8680
@tagesseassefa8680 29 дней назад
ዝም ብላ ተፈላሰፍ እንጂ ሐዋርያዊት ቤ/ክ lord(አብ),jesus -ወልድ እና christ -መንፈስ ብላ አታስተምርም።
@SelamawitGod-gl2we
@SelamawitGod-gl2we 3 месяца назад
Temehereteke batam teru nawo Orthodox yametasetameraw nawo
@andualemabera1123
@andualemabera1123 6 месяцев назад
ሰው ይህንን ሰምቶ ካላረፈ እራሱን ይመርምር
Далее