Тёмный

በባህር ዳር ከተማ በጸጥታ ኃይሎች ታስረው የነበሩት ሁለት የምክር ቤት አባላት ተለቀቁ |zena |ethiopiainsider 

Ethiopia Insider
Подписаться 54 тыс.
Просмотров 468
50% 1

በባህር ዳር ከተማ ከትላንት በስቲያ በጸጥታ ኃይሎች በቁጥጥር ስር የዋሉት የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) የፓርላማ አባል አቶ ዘመነ ኃይሉ እና በአማራ ክልል ምክር ቤት የብልጽግና ፓርቲ ተወካይ የሆኑት አቶ መልካሙ ተሾመ ከእስር ተለቀቁ። ሁለቱ የምክር ቤት አባላት ዛሬ ሐሙስ እኩለ ቀን ገደማ መፈታታቸውን አቶ ዘመነ ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” አረጋግጠዋል።
አቶ ዘመነ እና አቶ መልካሙ ከመስሪያ ቤታቸው በጸጥታ ኃይሎች የተወሰዱት ከትላንት በስቲያ ማክሰኞ መስከረም 21፤ 2017 ነበር። የፓርላማ አባሉ በቁጥጥር ስር ከመዋላቸው በፊት አንድ ቀን አስቀድሞ፤ በሚኖሩበት ቀበሌ ያሉ ኃላፊ እና ሰራተኛ ወደ ቤታቸው በመምጣት አድራሻቸውን እና በመታወቂያቸው ያሉ መረጃዎችን አጣርተው መሄዳቸውን ተናግረዋል።
ይህ የተደረገበት ምክንያት ለምን እንደሆነ ለቀበሌ ሰራተኞቹ ጥያቄ አቅርበው እንደነበር አቶ ዘመነ ገልጸዋል። በባህር ዳር ከተማ የአጼ ቴዎድሮስ ክፍለ ከተማ የጠይማ ቀበሌ ኃላፊ “አንዳንድ ነገር ማጣራት ፈልገን ነው። ስንፈልግ እንደውላለን” የሚል ምላሽ እንደሰጧቸውም አብራርተዋል።
ከዚህ ሁነት ማግስት “የታጠቁ የአማራ ክልል አድማ በታኝ አባላት” ከመስሪያ ቤታቸው እንደወሰዷቸው የፓርላማ አባሉ ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” አስረድተዋል። አቶ ዘመነ በአማራ መልሶ መቋቋም እና ልማት ድርጅት (አመልድ) ስር ባለው ዓባይ ኮንስትራክሽን ውስጥ የእቅድ ክትትል እና ህዝብ ግንኙነት ኬዝ ቲም አስተባባሪ በመሆን እየሰሩ ይገኛሉ።
የአብን የፓርላማ ተወካዩ በትላንትናው ዕለት አምስት ሰዓት ገደማ በስራ ገበታቸው ላይ እያሉ፤ በቁጥር ስምንት ገደማ የሚሆኑ የአማራ ክልል አድማ በታኝ አባላት ወደ ቢሯቸው መምጣታቸውን ተናግረዋል። “ቢሮ እንዳይረበሽ ወደ ውጭ ወጣሁ። እኔ ነኝ አልኳቸው። ‘ለኢንተርቪው ፈልገንህ’ ነው አሉኝ። እሺ ብዬ [ሄድኩ]” ሲሉ በወቅቱ የነበረውን ሁኔታ አስታውሰዋል።
አቶ ዘመነ መጀመሪያ በባህር ዳር ከተማ ወደሚገኘው ሙሉአለም የባህል ማዕከል መወሰዳቸውን እና ወደ አመሻሽ አካባቢ በከተማይቱ ወዳለው ዘጠነኛ ፖሊስ ጣቢያ መዘዋወራቸውን አብራርተዋል። እንደ እርሳቸው ሁሉ ከሚሰሩበት መስሪያ ቤት የዚያኑ ዕለት በጸጥታ ኃይሎች በቁጥጥር ስር ውለው የነበሩት የአማራ ክልል የምክር ቤት አባል አቶ መልካሙ ተበጀም በተመሳሳይ መልኩ ወደ ፖሊስ ጣቢያ መወሰዳቸውን አክለዋል።
(ኢትዮጵያ ኢንሳይደር)
ተጨማሪውን ለማንበብ ይሄን ሊንክ ይጫኑ ethiopiainside...
የ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ትኩስ ዜናዎችን እና ወቅታዊ ዘገባዎችን ለመከታተል፦
ድረ ገጽ ፦ ethiopiainsider...​
ፌስቡክ ፦ / ethiopiainsider
ትዊተር (ኤክስ) ፦ / ethiopiainsider
ቴሌግራም፦ t.me/EthiopiaI...
ቲክቶክ፦ / ethiopiainsider

Опубликовано:

 

7 окт 2024

Поделиться:

Ссылка:

Скачать:

Готовим ссылку...

Добавить в:

Мой плейлист
Посмотреть позже
Комментарии : 1   
Далее