እህት! "ሥሕተት ብቻ እየለቀማችሁ የኡስታዞችን ታወጣላችሁ ... ኡስታዞን ለማሠደብ" ስትይ የምትያቸዉን ነገሮች ለራስሽ ግናዛቤ ያለሽ አይመስልም። የዘነጋሽው ሥሕተት በሌለበት በባዶ ሜዳ ልብ ወለድ ድራማ የምትሠሪ በሚመስል ሁኔታ በዘፈቀደ እየተነሳሽ የተፈበረኩ ነጥቦች እያነሳሽ በኡስታዞችና በመጅሊሱ ላይ የምትለጥፊና ስማቸዉን እና ክብራቸዉን የምታጠፊ ቀንደኛ መሪ ነሽ! ለምሳሌም፡ አሁን በቅርብ እንክዋን ከሠላም ሚኒስቴር ጋር የመጅሊስ ተወካዮች ካድረጉት ዉይይት ላይ ተቆርጦ በሸፍጠኖች ከተለቀቀው ንግግራቸው ላይ ከተባለበት ምህዳር ዉጭ ሐሳቦችን ፈብርከሽ ሥማቸዉን በማጥፋት ዘርጥጠሻል። ኡስታዝ አህመዲን ጀበልን ተጨማሪ ደም እንዳይፈስ በቀብር ቦታ ተገኝቶ የማረጋጋት ንግግር ላይ ያልገባሽን ቃል አውጥተሽ (ተክቢር እንዴት ይከለክላል ብለሽ) ተችተሻል፣ እንዲሁም በስብሠባ ወቅት ተሳታፊ እንደነበርሽ በሚመስልnካሚል ሸምሱን የኦሮሚያ ፕረዚደንት ይቅርታ ጠየቀ ያለው ውሸቱን ነው ብለሽ በዉሸተኝነት ወንጅለሻል። "O you who have believed, why do you say that which you do not do? Most hateful it is in the sight of Allah that you should say that which you do not do. Allah indeed loves those who fight in His Way in ranks as though they were a solid wall." ሱራቱ-ሠፍ