በእውነት ሰማዕታት
በእውነት ሰማዕታት ምርጦችህ ሆኑ /2/ አዝ
የዓለምን መንግሥት ክብሩን ሁሉ ስለመነኑ
ተመተሩ ተቆራረጡ
ስለስምህ ብለው ያላቸውን ሁሉ እያጡ
ተቃጠሉ በሰይፍ አለቁ
የሚመጣውን ክብር መንግሥትህን ስለናፈቁ
ምድራዊውን መንግሥት ትተው
ወደ የማያልፈው ክብር ተጓዙ ከዓለም ወጥተው
ወደ ተኩላዎች መንጋ ተላኩ
ቃለ ወንጌልህን በአሕዛብ መንደር ሊሰብኩ
ወደ ሸንጎ አሳለፏቸው
በነገሥታቱ ፊት በአደባባይ ሊያስጨንቋቸው
በዚያች ሰዓት ሳይሳቀቁ
ለሚናገሩት ቃል ሳያስቡ ሳይጨነቁ
ጰራቅሊጦስ አፅናኝ ነውና
እስከ መጨረሻው ለታገሰ በእምነት ለፀና
መከራውን እያስቻላቸው
እግዚአብሔር የድልን ዘውድ አቀዳጃቸው
29 окт 2019