የየካቲት 66ቱ የኢትዮጵያ ሕዝባዊ አብዮት ዘውዳዊውን አገዛዝ ከገረሰሰ ዘንድሮ 50ኛ ዓመቱን ደፍኗል።
የንጉሡ ከሥልጣን መወገድ ‘ቁጣ ነው’ ብለው ያለቀሱና ‘ኢትዮጵያም አበቃላት’ ብለው በሐዘን የተዋጡ በአንድ ወገን ሲቆሙ ‘ኢትዮጵያ ቀን ወጣላት’ ብለው በደስታ የቦረቁና ‘በኅብረተሰባዊት ኢትዮጵያ’ መመሥረት ተስፋ የጣሉ በሌላ ወገን ቆመዋል።አብዮቱን መለስ ብለው ሲያስታውሱ፣ አብዮቱን ተከትሎ ሥልጣን የጨበጠውና ‘ደም እንደ ጅረት ያፈሰሰው’ ብለው የሚገልጹትን ወታደራዊው የደርግ አገዛዝ በስብራት የሚገልጹ ወገኖች፣ ‘ለዚህ ነበር የታገልነው?’ ብለው በቁጭት ይብከነከናሉ።
አብዮቱን በማቀጣጠል፣ ሕዝብን በማንቃትና በማደፋፈር፣ የለውጥ ድምጽ በመሆን፣ ከአብዮቱ በፊትና በኋላም አመራሮችን በመተቸት፣ ኢ-ፍትሐዊነትን ነቅሶ በማውጣት፣ ቀውሶች ሲፈጠሩ ሕዝብን በማጽናናትም ጥበብ ድርሻ ነበራት። አብዮቱም የኢትዮጵያን ጥበብ በቅርጽ እና በይዘት ለውጧል።
#tireka #ትረካ #amharicbooks #ethiopian #ትረካትዩብ #የአማርኛመፅሀፍት #በዕውቀቱስዩም #በዕውቀቱስዩም #አማርኛ #የአማርኛትረካ #የመጽሐፍትትረካ #ሸገር #ሸገርሼልፍ #መቆያ #amharic #ethiopianhistory #ethiopianmusic #ethiopia2024
20 мар 2024