ገና ባልተጠናቀቀው የኢትጵያ ቤትኪንግ ፕሪምየር ሊግ ቀሪ 9 ጨዋታዎች እየቀሩ አቡበከር ናስር ከወዲሁ 20 ጎሎችን በማስቆጠር የኮከብ ጎል አግቢነቱን በመምራት ላይ ይገኛል፡፡ አቡበከር በጌታነህ ከበደ የተያዘውን የ25 ጎል ክብረወሰን ለመስበር 6 ጎል የቀረው ሲሆን ይህንንም ለማድረግ በቂ ቀሪ ጨዋታ ያለው መሆኑ ይሰብረዋል የሚለውን ግምት ካለው የኢትዮጵያ ቡና ወቅታዊ አቋም እና የአቡኪ ድንቅ ብቃት ጋር የሰፋ ዕድል እንዲኖረው አስችሎታል፡፡
19 мар 2021