5 ቀን
ሕይወትን ከእግዚአብሔር እይታ አንፃር መልዕክት።
“…ሕይወታችሁ ምንድናት?...” ያዕ. 4-14
ለሕይወት ያለህ አተያይ ሕይወትህን ይቀርፀዋል።
ሕይወት የምትሰጠው ትርጉም፣ፍፃሜ እጣህን ይወስነዋል።
ሕይወት እይታህ በጊዜ ፣በገንዘብ ባለህ ተሰጥኦ አጠቃቀም እና ከሌሎች ጋር ላለህ ግንኙነት በምትሰጠው ዋጋ ላይ ተፅእኖ ይደረጋል።
ሕይወት እንዴት እንደምትሠራና ከሷ የምትጠብቀውን ምን መሆኑን የምትገልጥበትንም ነው።።
መጽሐፍ ቅዱስ የእግዚአብሔርን የሕይወት እይታ የሚያመለክቱ ሦስት ተምሳሌቶች ያቀርባል
1 ሕይወት ፈተና ነው
አዳምና ሔዋን በገነት ተፈትነው ወድቀዋል
ዳዊትም በብዙ ወድቆአል::
ዮሴፍ ፣ሩት ፣ አስቴር ፣ዳንኤል የመሳሰሉት ግዙፍ ፈተና አልፈዋል ።
ባህሪይ በፈተና አማካኝነት ያድጋል ።
“በሰዎች ሁሉ ላይ ከደረሰው የተለየ ፈተና አልደረሰባችሁም ፣እግዚአብሔር ታማኝ ነው ስለዚህ ከምትችሉት በላይ እንድትፈተኑ አይተዋችሁም ነገር ግን በምትፈተኑበት ጊዜ ፣ፈተናውን መታገስ እንድትችሉ፣መውጫ መንገዱን ያዘጋጅላችኃል።” 1ቆሮ 10/13
2 ሕይወት ባላደራነት ነው
ያልተቀበልክው የራስህ የሆነ ነገር ምን አለ ??
ከተቀበልህ ታዲያ እንዳልተቀበህ ለምን ትመካለህ ??1ቆሮ 4-7
እግዚአብሔር ይበልጥ በሰጠህ መጠን ይበልጥ ኃላፊነት የሚሰማህ እንድትሆን ይፈልጋል።
“በትንሹ የታመነ በብዙ ይሾማል” ሉቃ. 16-10
በሪክ ዋረን
አላማ መር ህይወት።
12 мар 2021