ቀን 1
ለምንድነው የተፈጠርኩት??
👉 የሁሉ ጀማሪ እግዚአብሔር ነዉ፡፡
ስለ አንተ አይደለም
የሕይወት አላማ ፣ከግል እርካታ ፣ከአእምሮ ሰላምና ከደስታህም ሁሉ የላቀ ነዉ፡፡
🔥ለምን እንደተፈጠርክ ማወቅ ከፈለክ እግዚአብሔርን በማወቅ ጀምር፡፡የተፈጠርከዉ በእግዚአብሔር ዓላማና ለእርሱ ዓላማ ነዉ፡፡
ምን ለመሆን ነዉ የምትፈልገው??የወደፊት ምኞቴ እያልን እራስ ተኮር ጥያቄዎች እናነሳለን፡፡በራሳችን ላይ በማትኮር የሕይወታችንን አላማ በፍፁም አይገልጥልንም፡፡
ኢዮብ 12:10
የሕያዋን ሁሉ ነፍስ
የሰዉም ሁሉ መንፈስ በእጁ ናት፡፡
የምትነኖረዉ እግዚአብሔር እንድትኖር ከመፍቀዱ የተነሳ ነዉ፡፡
የተፈጠርከዉ በእግዚአብሔር ለእግዚአብሔር ነዉ፡፡
ከእግዚአብሔር ብቻ ነዉ መነሻችንን ፣ ማንነታችንን የሕይወታችንን ትርጉም ፣ዓላማችንን ጠቃሚ ወይም አስፈላጊነታችንን እና የመጨረሻ መድረሻችንን ልናገኝ የምንችለው፡፡
✍️የህይወት ትርጉም እግዚአብሔር ለዓላማው እንዲጠቀምብህ መፍቀድ እንጂ ለራስህ ዓላማ እርሱን መጠቀሚያ ማድረግ አይደለም ፡፡
እግዚአብሔር ሲፈጥርህ እንድትሆንለት የፈለገውን ሆነህ ስለመገኘትህ የሚያስረዳ ነዉ፡፡
👌የተፈጠርከዉ በእግዚአብሔርና ለእግዚአብሔር ነዉ፡፡ይህንን ካልተገነዘብክ ሕይወት ትርጉም ያለዉ አይሆንም፡፡
እግዚአብሔር የሕይወትህ መነሻ ብቻ ሳይሆን የሕይወትህ ምንጭም ነዉ፡፡በመሆኑም የሕይወትህን ዓላማ ለመገንዘብ ትኩረትህን ወደ እግዚአብሔር ቃል አድርግ፡፡ወጀ አለም ጥበብ አይደለም፡፡
ኤፌ 1:11
እንደ ፈቃዱ ምክር ሁሉን የሚሰራ እንደ እርሱ ሃሳብ አስቀድመን
የተወሰንን በክርስቶስ ደግሞ እርስትን ተቀበልን፡፡
ማንነትህንና የሕይወት አላማ ከእየሱስ ክርስቶስ ጋር በሚኖርህ ግንኙነት ዓማካኝነት ታገኛለህ፡፡
ከ ሪክ ዋረን
ዓላማ መር ህይወት
28 фев 2021