በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚንቀሳቀሰው የቦሮ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (ቦዴፓ)፤ ከክልሉ መንግስት ጋር “አብሮ ለመስራት” ያሳለፈውን ውሳኔ እንደገና እንደሚያጤነው ገለጸ። ፓርቲው አብሮ የመስራቱን ሂደት ለማጤን የተገደደው በአባላቱ፣ በደጋፊዎቹ እና አመራሮቹ ላይ “ እስር፣ ዛቻ እና ማስፈራሪያ” እየደረሰባቸው በመሆኑ ምክንያት መሆኑን አስታውቋል።
ቦዴፓ ትላንት ማክሰኞ መስከረም 7፤ 2017 ባወጣው መግለጫ፤ ባለፈው ሰኔ ወር አጋማሽ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ከተደረገው ቀሪ እና ድጋሚ ምርጫ በኋላ በክልሉ “የዴሞክራሲ ምህዳር መጥበቡን” ጠቅሷል። ፓርቲው በዚሁ ምርጫ ሶስት የክልል ምክር ቤት እና አንድ የፓርላማ መቀመጫ በቡለን ወረዳ እና ሽናሻ ልዩ ምርጫ ክልሎች ላይ አሸንፏል።
ፓርቲው ለክልል እና ለፌደራል ምክር ቤቶች በተወዳደረባቸው የምርጫ ክልሎች ውስጥ በሚገኙ አባላቱ፣ ደጋፊዎቹ እና አመራሮቹ ላይ “የተቀናጀ ወከባ፣ እስራት፣ ድብደባ፣ ህገወጥ የስራ ዝውውር፣ መብት እና ጥቅም በመንፈግ” እየደረሰ እንደሚገኝም በመግለጫው ዘርዝሯል። ቦዴፓ “የፖለቲካ አመለካከትን መሰረት ያደረገ ጫና እያደረሱብኝ ነው” ሲል በመግለጫው የወነጀላቸው፤ በክልሉ ያሉ የገዢው ብልጽግና ፓርቲ አመራሮችን ነው።
(ኢትዮጵያ ኢንሳይደር)
ተጨማሪውን ለማንበብ ይሄን ሊንክ ይጫኑ ethiopiainside...
-------------------------------------------------------------------------------------------
የ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ትኩስ ዜናዎችን እና ወቅታዊ ዘገባዎችን ለመከታተል፦
ድረ ገጽ ፦ ethiopiainsider...
ፌስቡክ ፦ / ethiopiainsider
ትዊተር (ኤክስ) ፦ / ethiopiainsider
ቴሌግራም፦ t.me/EthiopiaI...
ቲክቶክ፦ / ethiopiainsider
7 окт 2024