Тёмный

የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ተቃዋሚ ፓርቲ፤ ከክልሉ መንግስት ጋር “አብሮ ለመስራት” ያሳለፈውን ውሳኔ እንደገና ለማጤን መገደዱን ገለጸ |ethiopiainsider 

Ethiopia Insider
Подписаться 54 тыс.
Просмотров 180
50% 1

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚንቀሳቀሰው የቦሮ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (ቦዴፓ)፤ ከክልሉ መንግስት ጋር “አብሮ ለመስራት” ያሳለፈውን ውሳኔ እንደገና እንደሚያጤነው ገለጸ። ፓርቲው አብሮ የመስራቱን ሂደት ለማጤን የተገደደው በአባላቱ፣ በደጋፊዎቹ እና አመራሮቹ ላይ “ እስር፣ ዛቻ እና ማስፈራሪያ” እየደረሰባቸው በመሆኑ ምክንያት መሆኑን አስታውቋል።
ቦዴፓ ትላንት ማክሰኞ መስከረም 7፤ 2017 ባወጣው መግለጫ፤ ባለፈው ሰኔ ወር አጋማሽ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ከተደረገው ቀሪ እና ድጋሚ ምርጫ በኋላ በክልሉ “የዴሞክራሲ ምህዳር መጥበቡን” ጠቅሷል። ፓርቲው በዚሁ ምርጫ ሶስት የክልል ምክር ቤት እና አንድ የፓርላማ መቀመጫ በቡለን ወረዳ እና ሽናሻ ልዩ ምርጫ ክልሎች ላይ አሸንፏል።
ፓርቲው ለክልል እና ለፌደራል ምክር ቤቶች በተወዳደረባቸው የምርጫ ክልሎች ውስጥ በሚገኙ አባላቱ፣ ደጋፊዎቹ እና አመራሮቹ ላይ “የተቀናጀ ወከባ፣ እስራት፣ ድብደባ፣ ህገወጥ የስራ ዝውውር፣ መብት እና ጥቅም በመንፈግ” እየደረሰ እንደሚገኝም በመግለጫው ዘርዝሯል። ቦዴፓ “የፖለቲካ አመለካከትን መሰረት ያደረገ ጫና እያደረሱብኝ ነው” ሲል በመግለጫው የወነጀላቸው፤ በክልሉ ያሉ የገዢው ብልጽግና ፓርቲ አመራሮችን ነው።
(ኢትዮጵያ ኢንሳይደር)
ተጨማሪውን ለማንበብ ይሄን ሊንክ ይጫኑ ethiopiainside...
-------------------------------------------------------------------------------------------
የ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ትኩስ ዜናዎችን እና ወቅታዊ ዘገባዎችን ለመከታተል፦
ድረ ገጽ ፦ ethiopiainsider...​
ፌስቡክ ፦ / ethiopiainsider
ትዊተር (ኤክስ) ፦ / ethiopiainsider
ቴሌግራም፦ t.me/EthiopiaI...
ቲክቶክ፦ / ethiopiainsider

Опубликовано:

 

7 окт 2024

Поделиться:

Ссылка:

Скачать:

Готовим ссылку...

Добавить в:

Мой плейлист
Посмотреть позже
Комментарии : 1   
@Non-e8j
@Non-e8j 17 дней назад
That area was mostly Amharas Begemdir province. When TPLF took power because strategically they have Oman to control benishangul just like they annexed Wolkait, Raya, Humera and afar land their plan was to control Benishangul they totally dismissed begemdir and started committing genocide against Amharas just like they did in Wolkait;(
Далее
PUBG MOBILE | Metro Royale: Fun Moments #4
00:16
Просмотров 343 тыс.