ሰብስክራይብ እና ሼር በማድረግ ለዳዕዋው ስፋት የበኩልዎን አስተዋጾ ያድርጉ። 💐
---
የኢየሱስ አምላክ
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡
መግቢያ
ቁርኣን ከወረደበት ምክንያት አንዱ የአዕምሮ ባለቤቶችም አላህ አንድ አምላክ ብቻ መኾኑን ሊያውቁበት ነው፦
14፥52 ይህ ቁርኣን ለሰዎች ገላጭ ነው፡፡ ሊመከሩበት፣ በእርሱም ሊያስጠነቅቁበት፣ እርሱም አንድ አምላክ ብቻ መኾኑን ሊያውቁበት፣ የአዕምሮ ባለቤቶችም ሊገሰፁበት የተወረደ ነው።
ነገር ግን ይህንን አንድ አምላክ አንዴ በማንነት ሶስት ነው፣ አንዴ ሰው ሆነ፣ አንዴ ለሰው ኀጢአት ሞተ እያሉ በነውርና በጎዶሎ ባህርይ ያሻርኩታል፤ ይህ አንድ አምላክ በመለኮታዊ ቅሪት ሲናገር እንዲህ ይላል፦
ሆሴዕ 11፥9 እኔ አምላክ ነኝ እንጂ ሰው አይደለሁምና፥
ኢሳይያስ 44:6 ከእኔ ሌላም አምላክ የለም።
አንዱ አምላክ እኔ አምላክ ነኝ እንጂ ሰው አይደለሁም፣ ከእኔ ሌላም አምላክ የለም እያለን ተመልሰው “ሰውም አምላክ ነህ” ማለት እኛ ፍጡራን፦ ፈጣሪን “ስለ አንተ ከአንተ ይልቅ እኛ እናውቅልሃለን” እያልነው ነው፤ ነገር ግን ኢየሱስ በአንዱ አምላክ እና በሰዎች መካከል መካከለኛ ሆኖ ከአምላክ ሰምቶ የሚናገር ሰው ነው፤ በድንቆች በምልክቶችም ከአንዱ አምላክ ዘንድ ለእስራኤል ሰዎች የተላከ ሰው ነበረ፦
1ኛ ጢሞቴዎስ 2:5 አንድ አምላክ Θεοῦ አለና፥ በአምላክ Θεοῦ እና በሰውም መካከል ያለው መካከለኛው ደግሞ አንድ አለ፥ እርሱም ሰው የሆነ ክርስቶስ ኢየሱስ ነው፤
ዮሐንስ 8፥40 ነገር ግን አሁን ከአምላክ Θεοῦ የሰማሁትን እውነት የነገርኋችሁን ሰው ልትገድሉኝ ትፈልጋላችሁ፤
የሐዋርያት ሥራ 2:22 የእስራኤል ሰዎች ሆይ፥ ይህን ቃል ስሙ፤ ራሳችሁ እንደምታውቁ፥ የናዝሬቱ ኢየሱስ አምላክ Θεοῦ በመካከላችሁ በእርሱ በኩል ባደረገው ተአምራትና በድንቆች በምልክቶችም ከአምላክ Θεοῦ ዘንድ ለእናንተ የተገለጠ ሰው ነበረ፤
እንግዲህ ኢየሱስ ሰው ከሆነ እና አንዱ አምላክ የላከው ከሆነ ሰው የሆነው ኢየሱስ እና አንዱ አምላክ ሁለት የተለያዩ ማንነት እና ምንነት ናቸው ማለት ነው፤ ኢየሱስ የሚያመልከው የራሱ አምላክ አለው፦
ነጥብ አንድ
“አምላኬ”
“አምላኬ” ማለት “የእኔ” አምላክ ማለት ነው፤ “አምላኬ” በሚል የመጀመሪያ መደብ “እኔ” የሚል አገናዛቢ ተውላጠ ስም አለ፤ “የእኔ አምላክ”my God” የሚለው የኢየሱስ ሙሉ እኔነት አምላክ አለው፦
ማቴዎስ 27:46 በዘጠኝ ሰዓትም ኢየሱስ፡- ኤሎሄ ኤሎሄ ላማ ሰበቅታኒ? ብሎ በታላቅ ድምፅ ጮኸ። ይህም፡- የእኔ አምላክ የእኔ አምላክ ፥ አንተ እኔን ስለ ምን ተውኸኝ? ማለት ነው። “”My God, my God, why have you forsaken me””.
ዮሐንስ 20:17 ኢየሱስም። ገና ወደ አባቴ አላረግሁምና አትንኪኝ፤ ነገር ግን ወደ ወንድሞቼ ሄደሽ። እኔ ወደ አባቴና ወደ አባታችሁ ወደ “አምላኬ” እና ወደ አምላካችሁ ዓርጋለሁ ብለሽ ንገሪአቸው አላት።
በተለይ ኢየሱስ አንዱን አምላክ “አንተ” እራሱን ደግሞ “እኔ” በማለት “አምላኬ” ማለቱ ሰው የሆነው ኢየሱስ እና አንዱ አምላክ ሁለት ህልውናዎች መሆናቸው ቁልጭ አድርጎ ያሳያል፤ “ተውከኝ” ስላለም በተወው ባለቤት እና በተተው ተሳቢ መካከል “ተውከኝ” የሚል ተሻጋሪ ግስ”transitive verb” መኖሩ ኢየሱስን ከአምላኩ ይለየዋል፤ በተጨማሪም “ወደ” የሚለው መስተዋድድ*preposition* መጠቀሙ በሁለት ማንነት መካከል ለመለየት የሚመጣ ነው፣ ኢየሱስ ማርያምን ወደ ወንድሞቼ ሄደሽ ማለቱ ወንድሞቹና ማርያም የተለያየ ማንነት እንዳላቸው እንደሚያሳይ ሁሉ “ወደ አምላኬ አርጋለው” ማለቱ አምላኩና ኢየሱስ ሁለት የተለያዩ ህላዌዎች መሆናቸውን ፍንትው አድርጎ ያሳያል። ኢየሱስ ካረገም በኃላ አብን አምላኬ ይላል፦
ራእይ 3፥2፤ ሥራህን በአምላኬ ፊት ፍጹም ሆኖ አላገኘሁትምና የነቃህ ሁን፥ ሊሞቱም ያላቸውን የቀሩትን ነገሮች አጽና።
ራእይ 3፥12 ድል የነሣው በአምላኬ መቅደስ ዓምድ እንዲሆን አደርገዋለሁ፥ ወደ ፊትም ከዚያ ከቶ አይወጣም፤ የአምላኬን ስምና የአምላኬን ከተማ ስም፥ ማለት ከሰማይ ከአምላኬ ዘንድ የምትወርደውን አዲሲቱን ኢየሩሳሌምን፥ አዲሱንም ስሜን በእርሱ ላይ እጽፋለሁ።
ነጥብ ሁለት
“አምላካችን”
ኢየሱስ “ወደ አምላኬ እና ወደ አምላካችሁ” አለ እንጂ “ወደ አምላካችን” ስላላለ አንዱ አምላክ ለኢየሱስ አምላክ የሆነበትና ለሃዋርያት አምላክ የሆነበት መደብ ይለያያል ይላሉ፤ ይህ ውሃ የማያነሳ ሙግት ነው፤ አንደኛ ይህ አነጋገር የተለመደ ነው፦
ዘፍጥረት 43፥23 እርሱም አላቸው፦ ሰላም ለእናንተ ይሁን፥ አትፍሩ፤ አምላካችሁ እና የአባታችሁ አምላክ በዓይበታችሁ የተሰወረ ገንዘብ ሰጣችሁ፤ ብራችሁስ ደርሶኛል።
“አምላካችሁ እና የአባታችሁ አምላክ” ስለተባለ አንዱ አምላክ ለአባታቸው ለያእቆብ እና ለልጆቹ አምላክነቱ ይለያያልን? ሁለተኛ ኢየሱስ “አምላካችን” በሚል አንደኛ መደብ ብዜት ተናግሯል፦
ኢሳይያስ61:1-2 የጌታ የእግዚአብሔር መንፈስ በእኔ ላይ ነው፥ ለድሆች የምሥራችን እሰብክ ዘንድ እግዚአብሔር ቀብቶኛልና፤ ልባቸው የተሰበረውን እጠግን ዘንድ፥ ለተማረኩትም ነጻነትን ለታሰሩትም መፈታትን እናገር ዘንድ ልኮኛል። የተወደደችውን የእግዚአብሔርን ዓመት “”አምላካችንም”” የሚበቀልበትን ቀን እናገር ዘንድ፥ የሚያለቅሱትንም ሁሉ አጽናና ዘንድ ልኮኛል፤
ማርቆስ 12:29 ኢየሱስም መልሶ እንዲህ አለው። ከትእዛዛቱ ሁሉ ፊተኛይቱ። እስራኤል ሆይ፥ ስማ፤ ጌታ “”አምላካችን”” አንድ ጌታ ነው፥
ነጥብ ሶስት
“አምላክህ”
መዝሙረኛ እግዚአብሔር ለኢየሱስ አምላክ መሆኑን ለማሳየት ” አምላክህ” በማለት በሁለተኛ መደብ ተናግሯል፦
መዝሙር 45:7 ጽድቅን ወደድህ ዓመፃንም ጠላህ፤ ስለዚህ ከባልንጀሮችህ ይልቅ እግዚአብሔር “አምላክህ” የደስታ ዘይትን ቀባህ።
ዕብራውያን 1:9 ጽድቅን ወደድህ ዓመፅንም ጠላህ፤ ስለዚህ እግዚአብሔር “አምላክህ” ከጓደኞችህ ይልቅ በደስታ ዘይት ቀባህ።
ለኢየሱስ ባለንጀሮቹ ሲቀቡ የነበሩት ነብያት ናቸው፤ ክርስቶስ ማለት “የተቀባ” ማለት ሲሆን አምላኩ እግዚአብሔር ኢየሱስን የደስታ ዘይት በሆነው በመንፈስ ቅዱስ ቀብቶታል፤ ቀቢው አንዱ አምላክ ከሆነ ተቀቢው ሰው ብቻ ነው፦
የሐዋርያት ሥራ 10:38 እግዚአብሔር የናዝሬቱን ኢየሱስን በመንፈስ ቅዱስ በኃይልም ቀባው፥ እርሱም መልካም እያደረገ ለዲያብሎስም የተገዙትን ሁሉ እየፈወሰ ዞረ፥ እግዚአብሔር ከእርሱ ጋር ነበረና፤
ነጥብ አራት
“አምላኩ”
ኢየሱስ አምላክ እንዳለው ለማሳየት “አምላኩ” በማለት በሶስተኛ መደብ ተናግረዋል፦
ራእይ 1:6 መንግሥትም “”ለአምላኩ”” እና ለአባቱም ካህናት እንድንሆን ላደረገ፥
ሚክያስ 5:4፤ እርሱም ይቆማል፥ በእግዚአብሔርም ኃይል “”በአምላኩ”” በእግዚአብሔር ስም ግርማ መንጋውን ይጠብቃል፤ እነርሱም ይኖራሉ፤ እርሱ አሁን እስከ ምድር ዳርቻ ድረስ ታላቅ ይሆናልና።
በተጨማሪም “የኢየሱስ ክርስቶስ አምላክ” በማለት ኢየሱስ አምላክ እንዳለው ተናግረዋል፦
ኤፌሶን 1:17 የክብር አባት የጌታችን “”የኢየሱስ ክርስቶስ አምላክ”” እርሱን በማወቅ የጥበብንና የመገለጥን መንፈስ እንዲሰጣችሁ እለምናለሁ።
2ኛ ቆሮንጦስ1:3 የርኅራኄ አባት የመጽናናትም ሁሉ አምላክ የሆነ የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አምላክና አባት ይባረክ።
2ኛ ቆሮንጦስ 11:31 ለዘላለም የተባረከ የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አምላክና አባት እንዳልዋሽ ያውቃል።
መደምደሚያ
[ሙሉ ጽሑፉን እዚህ ያገኙታል። t.me/Wahidcom ]
#የእየሱስ_ጌታ #JesusProphetOfAllah #Ustaz_Wahid_Omer
5 окт 2020