#የመዝሙሩ_ግጥም
🌼 🌼
🌼የእንቁጣጣሽ መዝሙር🌼
🌼 🌼
እሰይ /ደስ ደስ ይበላችሁ/(፪)
ቅዱስ ዮሐንስ መጣላችሁ
ደስ ደስ ይበላችሁ
ደስ ብሎን መጣን ደስ ብሎን(፪)
ጌቶች አሉ ብለን
ደስ ብሎን መጣን ደስ ብሎን(፪)
እሜቴ አሉ ብለን
አበባዮሽ 🌼 ለምለም
አበባዮሽ 🌼 ለምለም
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
እንቆቅልሽ - - ንግሥት
ልትፈትን ሄዳ - - ንግሥት
ንግስተ አዜብ - - ንግሥት
እናት ማክዳ - - ንግሥት
በልቧ ያለውን - - ንግሥት
አጫወታቸው - - ንግሥት
አሰቀምጣ አበባ- - ንግሥት
እያሳየችው - - ንግሥት
መአዛው የሚሸት - - ከሁለቱ
የቱ ነው አለቸው - - ከሁለቱ
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
ንግስት ሆይ ለጥያቄሽ ጥበብ አለሽ (*፪)
የአገር አድባር የሚሆነው ከልብ ሽተሽ(*፪)
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
እንቆቅልሹ - - የሳባ
ከበድም ቢለው - - የሳባ
ጥበብ ሰላለው - - ንጉሡ
ሚሥጥሩን ሊያውቀው - - ንጉሡ
ክፈት መስኮቱን - - ሰለሞን
ቢለው ለሎሌው - - ሰለሞን
ገቡ ንቦቹ - - ሊቀስሙ
ከአባባው አርፈው - - ሊቀስሙ
ብልህ ጠቢቡ - - መለሠ
ለተጠየቀው - - በእውነት
ንጉስ ሰለሞን - - አለ
አልተሠወረው - - በእውነት
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
አደይ ቅድስት ሀገሬ እልል በይ (*፪)
ኢትዩዮጲያ የዝና ስሟ በዓለም ተሠማ (*፪)
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
ለፈጣሪዋ - - ንግሥት
ምስጋና አቅርባ - - ንግሥት
ኢትዮጲያዊቷ - - ንግሥት
ንግስተ ሣባ - - ንግሥት
ጥበቡን አይታ - - ንግሥት
አደነቀችው - - ንግሥት
ወርቅ ሸቶውን - - ንግሥት
ዕንቁ ሰጠችው - - ንግሥት
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
ንግስት ሆይ ምስክር ሆንሽ ለሀገርሽ (፪)
የአምላክን የፈጣሪያችን ስሙን ጠርተሽ (*፪)
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
የኢትዮጵያ ሠዎች - - ለንግሥት
ቆሙ በተራ - - ለንግሥት
እደጅ ሆነው - - ለንግሥት
ለዙፋን ክብሯ - - ለንግሥት
በመስከረም ወር - - ለንግሥት
ሀገር ስትገባ - - ለንግሥት
ይዘው ሥጦታ - - ለንግሥት
የፈካ አበባ - - ለንግሥት
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
አደይ የብርሃን ጮራ በኢትዮጵያ በራ (፪)
ኢትዮጲያ በታሪክሽ ጥንታዊት ነሽ (፪)
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
ኢየሩሳሌም - - ንግሥት
ደርሠሽ መጣሽ - - ንግሥት
እንኳን በክብር - - ንግሥት
ለዚህ አበቃሽ - - ንግሥት
ከአምላክ በረከት - - ንግሥት
ፍሬ አግኝተሽ - - ንግሥት
የዘሽ ስጦታ - - ንግሥት
ዕንቁ ለጣጣሽ - - ንግሥት
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
ንግስት ሆይ ለታሪክሽ ክብር አለሽ (፪)
ልጆችሽ አበባዮሽ እያልን እናስታውስሽ (፪)
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
የአባቶች ተስፋ - - ለፃድቃን
የነቢያት ትንቢት - - ለፅናት
የሙሴ ፅላት - - ለፀሎት
የአሮን በትር - - ለፅናት
የዳዊት መንግስት - - ለፅናት
ይዘሸ የመጣሽ - - ከጥንት
አምስቱን አውታር - - ለሠጠሽ
ለሀገር መሠረት - በእውነት
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
አደይ ቅድስት ኢትዮጵያ እልል በይ (፪)
ኢትዮጵያ በልጆችሽ ደስ ይበልሽ (፪)
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
በህገ ልቦና - - ህጉን
ፈጣሪን አውቀሽ - - ህጉን
ህገ ነቢያትን - - ከዓለም
ፈጥነሽ ተቀበልሽ - - ከዓለም
በብሉይ ኪዳን - - ለጌታ
መስዋዕት አቅርበሽ - - ለጌታ
ተስፋ ካረጉት - - ከአይሁድ
ከአስራኤል - - ከአይሁድ
ህገ ወንጌልን- - በፊት
ይዘሽ ተገኘሽ - - በፊት
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
ኢትዮጵያ ደስ ይበልሽ ትልቅ ፀጋ አለሽ(፪)
ስለፈፀምሽ ሦስቱን ህግጋት ለፈጣሪሽ (፪)
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
ካለፈው ሰህተት - - ሁላችን
እንድንመለስ - - ሁላችን
አዲሱ ዓመት - - ለሁሉም
መጣ ማቴዎስ- - ለሁሉም
ይህም ያልፍና - - በጊዜው
ይመጣል ማርቆስ - - በጊዜው
ሌላው ይተካል - - በጊዜው
ዘመነ ሉቃስ - - በጊዜው
ወልደነጓድጓድ - - በጊዜው
ሲደርስ ዮሐንስ - - በጊዜው
በየአራት ዓመት - - በጊዜው
ለሁሉም ሲደርስ - - በጊዜው
በየዓመቱ - - መጥምቁ
ቅዱስ ዩሐንስ - - በጊዜው
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
አደይ የብርሃን ጮራ በዮሐንስ በራ(፪)
ኢትዮጵያ ባሕል ቋንቋሽ የሚያኮራሽ (፪)
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
ልጅ አበባ ልጅ አበባዬ
አዬ ውዲቷ እናቴ
ልጅ አበባ እያለች እማማ
አዬ ውዲቷ እናቴ
ምክሯን ሁሌ እኔ እንድሰማ
አዬ ውዲቷ እናቴ
እያሻሸች እንድሆን ጤናማ
አዬ ውዲቷ እማማ
አዬ ውዲቷ እናቴ (፪)
🌼አበባ ለምለም 🌼 ቀጤማ ለምለም
🌼ኢትዮጵያ እንዳንቺ የለም (፪)🌼
አብዬ ኧኸ ደግሞም እማምዬ
መጣሁ ለሰላምታ ከቤት አሉ ብዬ🌼
እንኳን ለቅዱስ ዮሐንስ አደረሰዎት ብዬ (፪)
🌼
ይሸታል ዶሮ ዶሮ (፪) ከማምዬ ጓሮ (፪)
ይሸታል የወይን ጠጅ (፪) ከጋሽዬ ደጅ (፪)
ከበረው ይቆዩ ከብረው 🌼
አመት አወደ አመት ደርሰው
ቅን ታዛዥ ልጅን ወልደው
ትሁት ሰው አክባሪ ሆነው
የፍቅር ሸማን ለብሰው🌼
ንስሐ ገብተው ቆርበው
🌼ከብረው ይቆዩ ከብረው
ዚቅ ሚድያ ZIQ MEDIA።
16 сен 2024