የአድዋ ጦርነት፡፡ ዝክረ አድዋ ልዩ ዘጋቢ ጥንቅር፡፡ The Battel of Adwa
አድዋ፣ ኢትዮጵያዊነት እንደገና በውበት፣ በምልአትና ጉልበት የተበየነበት፣ እያንዳንዱ መንደር ሰዎቹን ማግሮ አገሩን ያጠረበት፣ አፈሩን ያነጠረበት ልዩ ገድል ነው፡፡ ይህ ሀያል ክንውን፣ ኢትዮጵያውያን በዘውግ፣ በሀይማኖት፣ በአካባቢያዊ ማንነት፣ በግለሰብ ስግብግብ ፍላጎት ሳይቆሽሹ በቅድስና የጀገኑበት፣ ጾታና እድሜ ሳይለያቸው በብጽዕና የተሰዉበት፣ የቀደመ ቁርሾና የስልጣን ሽኩቻ ሳይነጣጥላቸው በንጽህና የከበሩበት ታሪካዊ ሁነት ነው፡፡
አድዋ ኢትዮጵያዊ በሞቱ ህይወትን፣ በህልፈቱ የሀገርን መቀጠል ያወጀበት ታላቅና እጹብ ተአምር ነው፡፡
አድዋ ለብዙ ሺህ አመታት የተሸመነው ኢትዮጵያዊ ማንነት ይበልጥ ያጌጠ የፈካበት፣ ይበልጥ ያማረ ያበበበት፣ አገራዊ ቃልኪዳን የታደሰበት፣ ፍትህ ግፍን የረታበት፣ ሰብአዊነትም ሁሉን ያሸነፈበት ታላቅ ችሎት ነው፡፡
እነሆ በደም የተዋጀ ነጻነታችንን ዋጋ እንገነዘብ ዘንድ፣ በመስዋእትነት የከበረ ማንነታችንን እናስብ ዘንድ፤ በህይወት ክፍያ የቆየ ታሪካችንን እናውቅ ዘንድ ይህንን ዝክር አዘጋጅተናል፡፡ ተሰውተው ያኖሩንን፣ ሞተው የጠበቁንን፣ ቆስለው ያዳኑንን አባት አያቶች እናመሰግን ዘንድ ይህንን ጥንቅር አሰናድተናል፡፡
ኢትዮጵያ በቀደመ እውነቷ ትድናለች፡፡
ኢትዮጵያ ምንጊዜም በክብር ትኑር፡፡
Share Like Subscribe
#Ethiopia #TheBattleofAdwa
27 авг 2024