ይህ ገጽ ወንጌልን መሠረት ያደረጉ ትምህርቶች የሚተላለፉበት ክርስቲያናዊ የዩቲዩብ ቻናል ነው።
የዚህ ቻናል ባለቤት በአንድ አምላክ በሦስት አካላት ማለትም በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ የሚያምን ፣ መዳን የሚገኘው በኢየሱስ ክርስቶስ ሞትና ትንሳኤ በማመንና የኢየሱስን ጌትነት በመመስከር ብቻ መሆኑን አጥብቆ ያምናል።
ዓላማ፦ ከመጽሐፍ ቅዱስ አስተምህሮ ውጪ ያሉ ሰዋዊ ትምህርቶችን በቃለ እግዚአብሔር መሠረትነት ማፍረስ እና ሰዎችን በእግዚአብሔር እውቀት ማሳደግ ነው ።
ቻናሉ የተገነባበት የመጽሐፍ ቅዱስ ምንባባት የሚከተሉት ናቸው ፦
“ በእግዚአብሔርም እውቀት እያደጋችሁ፥”
- ቆላስይስ 1፥10-11
“የሰውንም አሳብ በእግዚአብሔርም እውቀት ላይ የሚነሣውን ከፍ ያለውን ነገር ሁሉ እናፈርሳለን ለክርስቶስም ለመታዘዝ አእምሮን ሁሉ እንማርካለን፥” 2ኛ ቆሮ 10፥5
13 окт 2024