መጽሐፈ ዜና መዋዕል ካልዕ / የጸሎተ ምናሴ/
ምናሴ ማለት ማስረሻ ማለት ነው፡፡ ምናሴ የንጉሥ ሕዝቅያስ ልጅ ነው፡፡1ኛ ነገ.20÷1
ዋና ሃሳብ
ይህ መጽሐፍ የምናሴ ጸሎት ተብሎ ሲታወቅ የተጻፈበት ምክንያት ምናሴ ባዕድ አምልኮን እየተከተለ ከአሞራውያን ይልቅ ክፋት ሲያደርግ በእግዚአብሔር ቁጣ የአሦር ንጉሥ ወደ ባቢሎን ማርኮ በወሰደው ግዜ የደረሰበትን መከራ እና ግፍ ለእግዚአብሔር በማሳሰብ ያቀረበው ጸሎት ነው፡፡
ልዩ ጠቃሚ ሐሳቦች
ያቀረበው ጸሎት ፡- 2ኛ ነገ. 21÷1-8 ፣ 2ኛ ዜና 33÷1-10 ፣ ኤር.15÷4፣
የንጉሡ የምናሴ ጸሎት ባለ አንድ ምዕራፍ ነው፣
በ2ኛ 33÷18 ሙሉ በሙሉ ምናሴ የጸለየው ጸሎት ስለሚናገር በ 80 አሐዱ የቀኖና ቅዱሳት መጻሕፍት አቆጣጠር ከሁለተኛ ዜና መዋዕል ጋር አንድ ሆኖ ይቆጠራል፡፡
11 мар 2017