#ይህ_ዝማሬ_በዘመን_ፍፃሜ_እንደሚኖር_ሰው_ስለዘመኑ #የተረዳሁትንና_የሚሰማኝል_ሀሳብ_ጠቅለል_አድርጌ_
#ያቀረብኩበት_ዝማሬ_ነው:: ~መፅሐፍ በተሰ 4:13-18 እንደሚናገረው
ነገር ግን፥ ወንድሞች ሆይ፥ ተስፋ እንደሌላቸው እንደ ሌሎች ደግሞ እንዳታዝኑ፥ አንቀላፍተው ስላሉቱ ታውቁ ዘንድ እንወዳለን።
ኢየሱስ እንደ ሞተና እንደ ተነሣ ካመንን፥ እንዲሁም በኢየሱስ ያንቀላፉቱን እግዚአብሔር ከእርሱ ጋር ያመጣቸዋልና።
በጌታ ቃል የምንላችሁ ይህ ነውና፤ እኛ ሕያዋን ሆነን ጌታ እስኪመጣ ድረስ የምንቀር ያንቀላፉቱን አንቀድምም፤
ጌታ ራሱ በትእዛዝ በመላእክትም አለቃ ድምፅ በእግዚአብሔርም መለከት ከሰማይ ይወርዳልና፥ በክርስቶስም የሞቱ አስቀድመው ይነሣሉ፤
ከዚያም በኋላ እኛ ሕያዋን ሆነን የምንቀረው፥ ጌታን በአየር ለመቀበል ከእነርሱ ጋር በደመና እንነጠቃለን፤ እንዲሁም ሁልጊዜ ከጌታ ጋር እንሆናለን።
ስለዚህ እርስ በርሳችሁ በዚህ ቃል ተጽናኑ። #ኢየሱስይመጣል #ማራናታ #Maranata #jesusiscomingsoon #christianmusic #2024 #newgosplemusicvideo
ግጥምና ዜማ እየሩሳሌም ነጊያ
08/06/2015 Etc
ዘመኑም እንደሰዉ ትላንቱን ናፈቀ
ማብቂያው እንደደረሰ በድኑም አወቀ
ቀንና ወራቱ ዘመንና ዓመታት
ሊሻር በዘላለም ቀን ሲቀረው ጥቂት
ተጣደፈ ሁሉ በዛ ትርምሱ
በላይ በላዩ ላይ ፋታ እየነሱ
ሀዘንና ደስታ ነጭና ጥቁሩ
ሲፈራረቁበት ጥላና ሀሩሩ
አወይ ዘመን አወይ ጊዜ
አዚም ጥሎ ድንዛዜ
ማብቂያውን አውቆ ሲያዘናጋን
ላኑር ብሎ እያባበለ
1 መርቅዞ ድኖ አቁስሎ አክሞ
በርቶ እየጠፋ አግዞ አድክሞ
መላቅጥ አጥቶ ሲያደናግረን
ይህ ነው ሰንለው ወዲያ ሲጥለን
መጣ ስንለው ደግሞ ይሄዳል
አረፍን ባልን ፋታ ይነሳናል!
አወይ ዘመን አወይ ጊዜ
እንዳናልፈው በትካዜ
አሳስበን ከፍቶ ከዚያ
ምን ሊበጀው ከዚህ ወዲያ
2 እንባ ሳይደርቅ እልል ሲያስብለን
ጮቤ አስረግጦ ደረት ሲያስደቃን
ቅርቡን አርቆ ሲያኖረን ማዶ
እውነት በሀሰት ሙላት በባዶ
ግርምት በፍዘት ተገላቢጦሽ
የማይጨበጥ ማብራሪያ የለሽ!
አወይ ጊዜ አወይ ዘመን
ሰው ታውሮ ቀን ሲዘምን
በድን ቆሞ ፍጡር ሲዘምም
ግዑዝ ድኖ ነፍስ ሲታመም
3 ፃድቅ ታፍኖ ሀጥህ ሲለፍፍ
ጠቢቡ ቆሞ ሰነፉ ሲያልፍ
ታታሪው በርዶት ቀማኛ ሲሞቅ
ነውር አደባባይ ሜዳ ላይ ሲደምቅ
ግርምት በፍዘት ተገላቢጦሽ
የማይጨበጥ ማብራሪያ የለሽ!
አወይ ዘመን አወይ ጊዜ
እንዳናልፈው በትካዜ
አሳስበን ከፍቶ ከዚያ
ምን ሊበጀው ከዚህ ወዲያ
4 በዓመፃ ብዛት ፍቅር ቀዝቅዞ
ራስን በመውደድ ሰዉ ነውዞ
በእኔነት ገመድ ነፍሱ ተይዞ
በእንቶ ፈንቶ አእምሮ ደንዝዞ
ስል ሰሚ ጆሮ ዳባ ሲለብስ
በመንታ ምላስ ሀገር ሲታመስ
አወይ ዘመን አወይ ጊዜ
እንዳናልፈው በትካዜ
አሳስበን ከፍቶ ከዚያ
ልብ አንጥልም ከዚህ ወዲያ::
27 июн 2024