የማቴዎስ ወንጌል
ምዕራፍ 5
1 ሕዝቡንም አይቶ ወደ ተራራ ወጣ፤ በተቀመጠም ጊዜ ደቀ መዛሙርቱ ወደ እርሱ ቀረቡ፤
2 አፉንም ከፍቶ አስተማራቸው እንዲህም አለ።
3 በመንፈስ ድሆች የሆኑ ብፁዓን ናቸው፥ መንግሥተ ሰማያት የእነርሱ ናትና።
4 የሚያዝኑ ብፁዓን ናቸው፥ መፅናናትን ያገኛሉና።
5 የዋሆች ብፁዓን ናቸው፥ ምድርን ይወርሳሉና።
6 ጽድቅን የሚራቡና የሚጠሙ ብፁዓን ናቸው፥ ይጠግባሉና።
7 የሚምሩ ብፁዓን ናቸው፥ ይማራሉና።
8 ልበ ንጹሖች ብፁዓን ናቸው፥ እግዚአብሔርን ያዩታልና።
9 የሚያስተራርቁ ብፁዓን ናቸው፥ የእግዚአብሔር ልጆች ይባላሉና።
10 ስለ ጽድቅ የሚሰደዱ ብፁዓን ናቸው፥ መንግሥተ ሰማያት የእነርሱ ናትና።
11 ሲነቅፉአችሁና ሲያሳድዱአችሁ በእኔም ምክንያት ክፉውን ሁሉ በውሸት ሲናገሩባችሁ ብፁዓን ናችሁ።
12 ዋጋችሁ በሰማያት ታላቅ ነውና ደስ ይበላችሁ፥ ሐሴትም አድርጉ፤ ከእናንተ በፊት የነበሩትን ነቢያትን እንዲሁ አሳድደዋቸዋልና።
Matthew chapter 5 | sermon of the mount | Amharic audio Bible. Thanks, everyone for liking the video and Subscribing to our channel.
music: Jean Olivier: • EMOTIONAL ENDING - JEA...
18 сен 2024