የአብርሃም አምላክ የይስሐቅም ቤዛ (፪)
ወገኖቹን ሁሉ በራሱ ደም ገዛ (፪)
የሐሰት ምስክር አቁመው ከሰሱት (፪)
በሞት እንዲቀጣ ሁሉም ፈረዱበት(፪)
ጲላጦስ ገረፈው በሰንሰለት አሥሮ(፪)
ከሮማውዉ መንግሥት እንዲኖር ተባብሮ(፪)
ድንግል አልቻለችም እንባዋን ልትገታ(፪)
እያየች በመስቀል ልጇ ሲንገላታ(፪)
በብርሃን ዙፋን ላይ የቆሙት እግሮቹ(፪)
በችንካር ላይ ሆነው ምንም አልሰለቹ(፪)
የብርሃን አክሊልን ለሰማዕት ያደለ(፪)
የእሾህ አክሊል ደፍቶ ቀራንዮ ዋለ (፪)
12 окт 2024