በዚህ ዝግጅት ከፕሮፌሰር በረከት ሀብተስላሴ ጋር የተደረገው ቃለምልልስ ሁለተኛ ክፍል ቀርቧል፡፡ ዶክተር በረከት ሀብተስላሴ በኢትዮጵያ የንጉሰነገስት መንግስት በፍርድ ሚኒስቴር ምክትል ሚኒስትርነት፣ በተባባሪ ዳኛነትና ኋላም ጠቅላይ አቃቢ ህግ ሆነው የሰሩ ሲሆን፣ የሀረርጌ ገዥ የህግ አመአካሪና የሀረር ከተማ ከንቲባም ነበሩ፡፡ ዶክተር በረከት በ1966 ክረምት የተቋቋውወ የመርማሪ ልዩ ኮሚሽን አባልም ነበሩ፡፡
እንደኢትዮጵያችን አቆጣጠር ከ1967 በኋላደግሞ፣ ወደኤርትራ በረሀ በመግባት ከ ጋር ከመስራታቸውም በላይ፣ የኤርትራ ከኢትዮጵያ የመነጠል እንቅስቃሴ የተባበሩት መንግስታት ተወካይ እንዲሁም ከኤርትራ ሀገር መሆን በኋላም የኤርትራ ህገመንግስት አርቃቂ ኮሚሽን ሰብሳቢ ሆነው ሰርተዋል፡፡
በዚህ ክፍል፣ በልዩ መርማሪ ኮሚሽኑ በነበራቸው ሚና ዙርያ ከኮለኔል መንግስቱ ሀይለማርያም ስለቀረበባቸው ክስ፣ ስለ50ዎቹና 60ዎቹ የተማሪዎች እንቅስቃሴ እንዲሁም ስለአብዮቱ ተጠይቀዋል፡፡ በወቅቱ የግራ ፖለቲካ የአማራ ብሄር በተለይ የጭቆና አመንጪና ተግባሪ አድርጎ የመክሰስ ትርክት ነበራችሁ፡፡ በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ እርግጥ እንደብሄር ወይም በብሄሩ ምክንያት የጨቆነና የተጨቆነ ነበርን? የሚል ጥያቄም ተነስቶላቸዋል፡፡ በወጥነት ለፍትህ ለእውነትና ለመርህ መቆም አለመቆማቸውም ተሞግቷል፡፡
ቃለምልልሱን ያድምጡ፡፡ Share, Like Subscribe ያድርጉ፡፡
5 авг 2024