"በቸርነትህ ዓመታትን ታቀዳጃለህ" (መዝ. 65÷11)
ለመላው የሀገራችን ኢትዮጵያ ህዝቦች፣ በሀገር ውስጥም ከሀገር ውጭ ላላችሁ ለሁሉም ህዝበ ክርስቲያን፣ እንኳን ለ2015 ዓ.ም የዘመን መለወጫ :በሠላም አሸጋገራችሁ/ አሸጋገረን!
የታመሙትን በስሙ የሚፈውስ፤ የተራቡትን በቸርነት የሚያጠግብ፤ የተጠሙትን በሕይወት ውሃ የሚያረካ፤ የታረዙትን በበጎ የሚያስብ የሚያለብስ፤ የታሰሩትንም የሚያጽናና፡ የሚጎበኝ፣ ክረምትንና በጋን የሚለዋውጥ፣ ዘመንን በዘመን የሚተካ፣ በዘመናት መቀያየር መሃል እርሱ ብቻ የማይለወጥ፣ አባት እንደሌላቸው ለብቻችን የማይተወን የፍጥረታት ሁሉ ጌታ ሕያው እግዚአብሔር አምላካችን በመለኮታዊ ጥበቃው ጠብቆ ከዘመን ወደ ዘመን ስላሸጋገረን ክብርና ምሥጋና፣ አምልኮ እና ውዳሴ ለስሙ ይሁን! አሜን ከመልአከ መንክራት ግርማ ወንድሙ
Subscribe, Share, Like, እያደረጋችሁ ላልሰሙት አሰሙ ላልነቁ አንቁ! መንፈሳዊነት ይብለጥ
9 сен 2022