አቶ በረከት ስምኦን ለርዕዮት ቃለምልልስ ለመስጠት የገቡትን ቃል አጠፉ፡፡
ውድ ታዳሚዎቻችን፣ ሰሞኑን አቶ በረከት በየመገናኛ ብዙሀን እየወጡ የመግለጫ ዘመቻ ማድረጋቸውን ተከትሎ እጅግ በርካታ ተከታታዮቻችን ርዕዮት ከአቶ በረከት ስምኦን ጋር ቃለምልልስ እንዲያካሂድ ጠይቃችሁናል፡፡ ይህንን በመመርኮዝናአቶ በረከት ሊቀርቡላቸው የሚገቡ እውነተኛ ጥያቄዎች መኖራቸውን በመረዳት ከቀናት በፊት እርሳቸው ጋር ደውለን ቃለምልልስ እንዲሰጡን ጠየቅን፡፡ ፈቃደኝነታቸውን ገልጸው ቃለምልልሱ ዛሬ August 31 2018 ከምሽቱ 3 ሰአት ላይ ሊደረግ ቀጠሮ ከሰጡን በኋላ በቀጠሮው መሰረት ስንደውል ቃላቸውን አጥፈው ቃለምልልሱን ሊሰጡን እንደማይችሉ ገልጠውልናል፡፡
የተሟላ “እውነት” አለኝ ሲሉ የከረሙት አቶ በረከት የእውነታቸውን ምልአት ምን ሰለቀጠው ይሆን? በጠመንጃ ካልሆነ በሀሳብ ድጋፍ ሊቆም አቅም የሌለው “እውነት”፡፡ ይደንቃል፡፡
ይህንን የአቶ በረከትን ጉዳይ ጨምሮ፣ በአዲስአበባችን ሊሰራ ስለታቀደው የእቴጌ ጣዪቱ ሀውልት ጉዳይና ሌሎች አገራዊ ጭብጦችን በቅዳሜ September 1 2018 የዜና መጽሄታችን ከ12 P.M አንስቶ የምንዳስስ በመሆኑ ቀጠሮአችሁን ከርዕዮት ጋር እንድታደርጉ ይሁን፡፡
እናመሰግናለን፡፡
30 авг 2018