ለመጠጥ ከ መቶ ሺህ ብር በላይ እንዲያወጣ እየጠጣ ባለቤቱን እንዲያስቸግር የሚያደርገው ክፉ መንፈስ አሰራሩ ሲጋለጥ በመልአከ መንክራት መምህር ግርማ ወንድሙ
ይሄ ሲሆን ታዲያ፤ እግዚአብሔር አምላክ ትውልዱን አምልኮት ያሰለጥነው ዘንድ በማኅበራዊ ሚዲያ ውስጥ ቃሉን ይዞ መጣ፡፡ አሁን እንዲህ ስል ዘልማዳዊ ግንዛቤ የሚባለው የሕይወት ጣዖት መካከል የቆዩ ሰዎች ሕሊና ውስጥ በእርግጠኝነት የተቃውሞ አሳብ ሊንሸራሸር ይጀምራል፡፡ "ይቀልዳል እንዴ? ጭራሽ እግዚአብሔር አምላክ በሚዲያ መጣ ይላል እንዴ? ሰማያዊ ቃል የሚነገርባት ቤተክርስቲያን እያለች ደሞ እግዚአብሔር በሚዲያ መጥቷል ይላል እንዴ" የሚሉ ለተቃውሞ የሚቸኩል ልብና እይታ ያላቸው ብዙ ሰዎች አሉ፡፡ ሁለቴ አሰቦ አንዴ መናገር የሚባለው የአባቶቻችን የማስተዋል መንገድ ከአእምሮአችን ተፍቆ አንዴ አስቦ ሁለቴ መናገር በሚል የግንፍልተኝነት ማእበል የተዋጥን ትውልዶች ስለሆንን፤ ክፉው መንፈስ የንቃተ ሕሊናችንን አድማስ አጥብቦ ኩርንችት የሆነ አመለካከት እንዲኖረን ዕድላችንን ከበጎ ጉዳይ ላይ እየጋረደ ክፉ ክፉው ላይ ይከፍተዋል፡፡
እውነታው ግን ይሄው ነው፡፡ ከመቼውም ጊዜ በላይ የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔርና ሰማያዊያኑ ቅዱሳን በሚዲያ በኩል ሊመልሱን እጃቸውን የዘረጉበት ዘመን ነው፡፡ ይህ እንዴት ሆነ ስንል፤ አስቀድሞ ዲያቢሎስና ሠራዊቱ በሚዲያው በኩል በሰፊ አድማስና በጥልቅ አያያዝ ሕዝቡን ተቆጣጥረውታልና፤ እስራትን ለመፍታት ማሰሪያው ቦታ ጋር መሄድ ስለሚያስፈልግ፤ ክፉው በበዛበት ቦታ ላይ ሰማያዊ ኃይል ይገለጥ ዘንድ የአምልኮት ትምህርት በሶሻል ሚዲያው እየተሰጠ ይገኛል፡፡
Subscribe, Share, Like, Comment እያደረጋችሁ ላልሰሙት አሰሙ ላልነቁ አንቁ! መንፈሳዊነት ይብለጥ! የማዳመጥ ጊዜ ላይ ነን!!!
29 окт 2020