የበሃይሉ ገናና ጥምቀት በልጅነት
ሰላም የአትሮኖስ ታዳሚያን፣ ዛሬ የልጅነቱን ገናንና ጥምቀትን ዘርዘር አድርጎና በውበት የሚያጫውተንን እንግዳ ይዘናል፡፡ እንግዳችን አቶ በሃይሉ ገብረመድህን ይባላል፡፡ ድንቅ የልጅነት ጊዜውን ዛሬ በአትሮኖስ ይገልጣል፡፡
አቶ በሃይሉ እስታትስቲሺያንና ዴሞግራፈር ነው፡፡ በአሁን ወቅት በተባበሩት መንግስታተ የህዝብ ፈንድ (UNFPA) የክትትልና ግምገማ ባለሞያ ሆኖ በመስራት ላይ ነው፡፡ ከዚያ አስቀድሞ ደግሞ በብሄራዊ የእስታትስቲክስ ባለስልጣን መስሪያቤት ለ25 አመታት አገልግሏል፡፡ ክቡራትና ክቡራን በሀይሉን አንተ ያልኩት አስፈቅጄ ነው፡፡ በሃይሉ የተወለደው ሻሸመኔ፣ ያደገው ደግሞ ጉምጉማ ነው፡፡
ለኪነጥበብ ባለው ልዩ ፍቅር፣ የስነህዝብን ጉዳዮች ማንም ሰው ሊረዳውና ሊማረክበት በሚችል መንገድ በተዋበ መልኩ እመድረክ ላይ ለብዙሀን በሚያቀርብበት ለዛና ጨዋታ ይታወቃል፡፡ እናም ዛሬ ገናና ጥምቀቱን ያወጋናል፡፡ ልጅነቱንም በርቱእ አንደበት፣ በሚጥም ለዛ ያጋራናል፡፡ ዝግጅቶቻችንን ሼርና ላይክ፣ ቻነላችንንም ሰብስክራይብ ማድረግ አትርሱ፡፡ አትሮኖስ ይቀጥላል፡፡
12 янв 2017